(ሃብታሙ ድረስ)
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ከ20 እስከ 25 ኪ.ግ ክብደት ያለው መካከከለኛ ሳተላይት ባለቤት የሚያደርጋትን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመች፡፡
ስምምነቱ የተፈረመው በእንጠጦ ኦብዞርቫቶሪና ምርምር ማዕከልና ፊንላንድ ከሚገኘው የኖርዲክ ሀገራት ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂና ሳይንስ ተቋም ጋር ነው፡፡
የስምምነቱ ዓላማ ደግሞ መሬትና ህዋን የሚመለከት ሳተላይት በትብብር መገንባትና ማምጠቅ ነው፡፡
የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን በላይ በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ የራሷን ሳተላይት ማምጠቋ ለእርሻ ስራ፣ ለተፈጥሮ ሃብት መቆጣጠሪያ፣ የአየር ንብረት ለመተንበይ፣ ስለማዕድን፣ ስለከተማ ልማትና ሌሎችም አገልግሎቶች ይጠቅማታል ብለዋል፡፡
የኖርዲክ ሀገራት ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂና ሳይንስ ተቋም ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ሳሊ አህመድ በበኩላቸው ተቋማቸው ያለውን የ50 አመታት ልምድ በመጠቀም በኢትዮጵያ ውጤታማ ስራ ለማከናወን መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
የእንጦጦ ህዋ ሳይንስ ኦብዘርቫቶሪ ተቋም ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ዋልዋ ኢትዮጵያ ለህዋ ሳይንስ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው ብለዋል፡፡
የአሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ቻይናና ሌሎች ሀገራት ተመራማሪዎች ከኢትዮጵያ ጋር በዘርፉ ለመስራት ፍላጎት ማሳየታቸውንም አቶ ተፈራ ገልጸዋል፡፡
*******
Source: ኢቲቪ፣ ነሐሴ 26፣ 2006
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…