Categories: EthiopiaNewsOromia

የአዲስ አበባ አዳማ የፈጣን መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ

ከአስር ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአዲስ አበባ አዳማ የፈጣን መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን እንዳስታወቀው፥ ከ10 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የወጣበት መንገዱ በዘመናዊነቱ በአገሪቱ የመጀመሪያው ነው ።

ከቻይና ኤግዚም ባንክ በተገኘ ብድርና በኢትዮጵያ መንግሥት በተያዘለት በጀት ነው ግንባታው የተካሄደው።

80 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአዲስ አዳማ የፈጣን መንገድ 31 ሜትር ስፋት ሲኖረው፥ በአንድ ጊዜም በግራና በቀኝ ስድስት ተሽከርካሪዎችን ያስተናግዳል።

መንገዱ በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ  አዳማ  ለመጓዝ  የሚወስደውን ከአንድ ሰዓት  የበለጠ ጊዜን  ወደ 40  ደቂቃ  የሚያሳጥር ነው ።

በቀን እስከ 20 ሺህ ተሽከርካሪ በሚያስተናግደው ነባሩ የአዲስ አበባ  አዳማ መንገድ  ላይ የሚስተዋለው የትራፊክ መጨናነቅና  አደጋን ይህ ፈጣን  መንገድ  የሚያስቀር ይሆናል።

በመስከረም 2003 ዓ.ም. ግንባታው የተጀመረው መንገዱ  ስምንት ትልልቅ ድልድዮችን፣ ከ77 በላይ አነስተኛ ድልድዮችን፣ 43 የሚደርሱ የእግረኛና የተሽከርካሪ መተላለፊያዎች የተገነቡለት፥ 80 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ አለው፡፡

የመንገዱን  ግንባታ  ያከናወነው የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ ነው።
*******
ምንጭ፡- ፋና – መጋቢት 27፣ 2006

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago