የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን እንዳስታወቀው፥ ከ10 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የወጣበት መንገዱ በዘመናዊነቱ በአገሪቱ የመጀመሪያው ነው ።
ከቻይና ኤግዚም ባንክ በተገኘ ብድርና በኢትዮጵያ መንግሥት በተያዘለት በጀት ነው ግንባታው የተካሄደው።
80 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአዲስ አዳማ የፈጣን መንገድ 31 ሜትር ስፋት ሲኖረው፥ በአንድ ጊዜም በግራና በቀኝ ስድስት ተሽከርካሪዎችን ያስተናግዳል።
መንገዱ በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ አዳማ ለመጓዝ የሚወስደውን ከአንድ ሰዓት የበለጠ ጊዜን ወደ 40 ደቂቃ የሚያሳጥር ነው ።
በቀን እስከ 20 ሺህ ተሽከርካሪ በሚያስተናግደው ነባሩ የአዲስ አበባ አዳማ መንገድ ላይ የሚስተዋለው የትራፊክ መጨናነቅና አደጋን ይህ ፈጣን መንገድ የሚያስቀር ይሆናል።
በመስከረም 2003 ዓ.ም. ግንባታው የተጀመረው መንገዱ ስምንት ትልልቅ ድልድዮችን፣ ከ77 በላይ አነስተኛ ድልድዮችን፣ 43 የሚደርሱ የእግረኛና የተሽከርካሪ መተላለፊያዎች የተገነቡለት፥ 80 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ አለው፡፡
የመንገዱን ግንባታ ያከናወነው የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ ነው።
*******
ምንጭ፡- ፋና – መጋቢት 27፣ 2006
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…