Categories: Ethiopia

ሰማያዊ ፓርቲ 250 ገደማ ሰዎች የተገኙበት ሰልፍ አካሄደ

(በታደሰ ብዙ አለም)

ፓርቲው በጃን ሜዳ ሰለማዊ ሰልፉን እንዲያካሂድ ቢፈቀድለትም ስፍራውን በመተው የፖርቲው ፅህፈት ቤት አድራሻ ባለበት የግንፍሌ አካባቢ ነው ያካሄደው።

በሰልፉ ላይ በግምት ከ220 እስከ 250 የሚደርሱ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ፥ የታሰሩ እስረኞች ይፈቱ ፣ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይግባ የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ታይተዋል።

የፓርቲው ሊቀ መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት እንደሚሉት ፥ ፓርቲያቸው መጀመሪያ ለከተማ አስተዳደሩ በፃፈው የማሳወቂያ ደብዳቤ ሰልፉን በመስቀል አደባባይ እንደሚያደርግ ነው።

ሆኖም አስተዳደሩ ፓርቲያቸው ሳያውቀው ሰልፉን ወደ ጃን ሜዳ እንደቀየረባቸው ነው የሚናገሩት።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው ግን ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የማሳወቂያ ደብዳቤ ባስገባበት ዕለት የሰልፉ ቦታ በጃን ሜዳ እንደሚሆን ምክንያቱ ተጠቅሶ ተነግሮታል ብለዋል።

መስቀል አደባባይ አሁን እየተካሄደበት ካለው የባቡር መስመር ዝርጋታና ከትራፊክ መጨናነቅ ጋር በተያያዘ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያካሄድበት መፍቀድ ተገቢ ነው ተብሎ በአስተዳደሩ እንዳልታመነበት አቶ አባተ የገለጹት።

ሰማያዊ ፓርቲም ሰልፉን በመስቀል አደባባይ ለማድረግ ጥያቄ ሲያቀርብ መልሱ ከነበቂ ምከንያቱ ቢገለጸለትም ፓርቲው ሆን ብሎ ተጨባጨ ያልሆነ የተዛባ መረጃ እያሰራጨ እንደሆነም ነው የተናገሩት

አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ በግልጽ እየታየ ፓርቲው መንገድ በመዝጋትና ትራፊክ በማጨናነቅ አጃቢ ለማግኘት ከማለም የተነሳ መስቀል አደባባይ አልተፈቀደለኝም የሚል ክስ እያስተጋባ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

**********

Source: Fana – Sept. 22. 2013

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

7 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

7 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

7 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

7 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

7 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

7 years ago