(በታደሰ ብዙ አለም)
ፓርቲው በጃን ሜዳ ሰለማዊ ሰልፉን እንዲያካሂድ ቢፈቀድለትም ስፍራውን በመተው የፖርቲው ፅህፈት ቤት አድራሻ ባለበት የግንፍሌ አካባቢ ነው ያካሄደው።
በሰልፉ ላይ በግምት ከ220 እስከ 250 የሚደርሱ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ፥ የታሰሩ እስረኞች ይፈቱ ፣ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይግባ የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ታይተዋል።
የፓርቲው ሊቀ መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት እንደሚሉት ፥ ፓርቲያቸው መጀመሪያ ለከተማ አስተዳደሩ በፃፈው የማሳወቂያ ደብዳቤ ሰልፉን በመስቀል አደባባይ እንደሚያደርግ ነው።
ሆኖም አስተዳደሩ ፓርቲያቸው ሳያውቀው ሰልፉን ወደ ጃን ሜዳ እንደቀየረባቸው ነው የሚናገሩት።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው ግን ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የማሳወቂያ ደብዳቤ ባስገባበት ዕለት የሰልፉ ቦታ በጃን ሜዳ እንደሚሆን ምክንያቱ ተጠቅሶ ተነግሮታል ብለዋል።
መስቀል አደባባይ አሁን እየተካሄደበት ካለው የባቡር መስመር ዝርጋታና ከትራፊክ መጨናነቅ ጋር በተያያዘ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያካሄድበት መፍቀድ ተገቢ ነው ተብሎ በአስተዳደሩ እንዳልታመነበት አቶ አባተ የገለጹት።
ሰማያዊ ፓርቲም ሰልፉን በመስቀል አደባባይ ለማድረግ ጥያቄ ሲያቀርብ መልሱ ከነበቂ ምከንያቱ ቢገለጸለትም ፓርቲው ሆን ብሎ ተጨባጨ ያልሆነ የተዛባ መረጃ እያሰራጨ እንደሆነም ነው የተናገሩት
አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ በግልጽ እየታየ ፓርቲው መንገድ በመዝጋትና ትራፊክ በማጨናነቅ አጃቢ ለማግኘት ከማለም የተነሳ መስቀል አደባባይ አልተፈቀደለኝም የሚል ክስ እያስተጋባ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
**********
Source: Fana – Sept. 22. 2013
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…