ሱዳን በፕሬዝዳንት አልበሽር አነሳሽነት የታላቁን መሪ መለስ ዜናዊን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ነሀሴ 18/2005 ዓ.ም በሱዳን የወዳጅነት አዳራሽ ልታከብር ነው፡፡
የመታሰቢያ ስነስርአቱ አስተባባሪ ኮሚቴ በኢንቨስትመንት ሚኒስትሩ ዶክተር ሙስጠፋ ኦስማን የሚመራ ሲሆን በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደርም የአስተባባሪ ኮሚቴው አባል ናቸው፡፡
ስነስርዓቱን ዛይን ቴሌኮሙኒኬሽን ካምፓኒ ስፖንሰር ያደርገዋል ተብሏል፡፡
ፕሮግራሙ ላይ ታላቁ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ በአፍሪካና በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ስለነበራቸው ሚናና በኢትዮ-ሱዳን ግንኙነት ላይ ስለነበራቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የተዘጋጁ ፅሁፎች ይቀርባሉ፡፡
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ለፕሮግራሙ ለመሳተፍ ወደ ካርቱም ያመራልም ተብሏል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሱዳን ፕሬዝዳንት ኦማር ሃሰን አልበሽር በታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ለመገኘት ነገ ነሃሴ 13/2005 ዓ.ም አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል ሱዳን ቪዥን ዘግቧል፡፡
**********
Source: ERTA – Aug. 18, 2013, titled “ሱዳን የታላቁን መሪ መለስ ዜናዊ 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ልታከብር ነው”
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…