የሱዳን መንግስት የመለስን ሙት ዓመት መታሰቢያ ያዘጋጃል

ሱዳን በፕሬዝዳንት አልበሽር አነሳሽነት የታላቁን መሪ መለስ ዜናዊን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ነሀሴ 18/2005 ዓ.ም በሱዳን የወዳጅነት አዳራሽ ልታከብር ነው፡፡

የመታሰቢያ ስነስርአቱ አስተባባሪ ኮሚቴ በኢንቨስትመንት ሚኒስትሩ ዶክተር ሙስጠፋ ኦስማን የሚመራ ሲሆን በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደርም የአስተባባሪ ኮሚቴው አባል ናቸው፡፡

ስነስርዓቱን ዛይን ቴሌኮሙኒኬሽን ካምፓኒ ስፖንሰር ያደርገዋል ተብሏል፡፡

ፕሮግራሙ ላይ ታላቁ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ በአፍሪካና በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ስለነበራቸው ሚናና በኢትዮ-ሱዳን ግንኙነት ላይ ስለነበራቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የተዘጋጁ ፅሁፎች ይቀርባሉ፡፡

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ለፕሮግራሙ ለመሳተፍ ወደ ካርቱም ያመራልም ተብሏል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሱዳን ፕሬዝዳንት ኦማር ሃሰን አልበሽር በታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ለመገኘት ነገ ነሃሴ 13/2005 ዓ.ም አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል ሱዳን ቪዥን ዘግቧል፡፡

**********

Source: ERTA – Aug. 18, 2013, titled “ሱዳን የታላቁን መሪ መለስ ዜናዊ 1ኛ ዓመት መታሰቢያ ልታከብር ነው”

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago