(ሰኢድ አለሙ)
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና በስሩ ተጠሪ የሆኑ ስድስት አጀንሲዎችን የ9 ወራት የስራ አፈጻጸም ገምግሟል፡፡
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር አቶ ሶፊያን አህመድ በሪፖርታቸው እንዳመለከቱት በዚህ አመት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ እንዲሁም በአገልግሎት ዘርፎች እየታዩ ያሉ ለውጦች 11.3 በመቶ ሀገራዊ እድገቱን ለማ
የዋጋ ንረቱን ወደ 6.1 በመቶ ማውረድም እንደተቻለና መንግስት መሰረታዊ ሸቀጦችን ከውጭ እያስመጣ ገበያውን ለማረጋጋት ባደረገው ጥረትና ከብሄራዊ ባንክ ብድር ባለመውሰድ ነው የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚውን መስመር ማስያዝ እንደተጀመረ ሚኒስትር ሶፊያን የተናገሩት፡፡
ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች 2.2 ቢሊዮን ዶላር ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ 77 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧል፡፡
ሚኒስትር ሶፊያን እንዳሉት ከአበዳሪዎች ቃል ከተገባው 64 ቢሊዮን ብር ውስጥ 32 ቢሊዮን ብር መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ በወጪ አሸፋፈን የ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ጉድለት ታይቷል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ አለማየሁ ጐጂ ክፍተቱን ለመሙላት ከመንግስት ግምጃ ቤትና ሌሎች አማራጮች ጥቅም ላይ ውለዋል ብለዋል፡፡
የበጀትና ፋይናንስና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዋና ወጎ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ወጥ አሰራርን ከመዘርጋት አንስቶ የቁጥጥርና ክትትል በማድረግ ችግሮቹን እየቀረፈ የመንግስትን የፋይናንስ አፈጻጻምን የበለጠ ማጠናከር እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
እንዲሁም የመንግስትን የፋይናንስ አፈጻጻም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር እየታየበት ያለውን የማስፈጸም አቅም ውስንነት ሊቀርፍ እንደሚገባም ምክር ቤቱ አሳሰቧል፡፡
***********
Source: ERTA – May 25, 2013
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…