በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ሲፈለጉ የነበሩት የናዝሬት ጉሙሩክ የህግ ማስከበር ኃላፊ አቶ ተመሰገን ጉልላት በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
ሰሞኑን በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎቸ ጋር ሲፈለጉ የነበሩት ግለሰቡ ከአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ በመሸሽ ሱዳን ለመግባት ሁኔታዎችን ሲያመቻቹ ነበር፡፡
ተጠርጣሪው በእጃቸው የተለያዩ ሰነዶችና 160 ሺህ ብር ይዘው ነበር የተሰወሩት፡፡ የጋምቤላ ጉሙሩክ ስራ አስኪያጅ ለሆኑት አቶ ጌታቸው አሰፋ 80 ሺህ ብር በመስጠት ወደ ሱዳን ለመግባት ጥረት አድርገዋል፡፡
ሆኖም ግን በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉች ትብብር ዋንኛ ተፈላጊ የነበሩት አቶ ተመስገን ጉልላትም ሆኑ እሳቸውን ወደ ሱዳን ለማስገባት የተባበሯቸው አቶ ጌታቸው አሰፋ በቁጥጥር ሰር መዋላቸውን ኢሬቴድ ከፖሊስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
*************
Source: ERTA
Check the Melaku Fenta et al saga archive for previous posts.
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…