(በላይ ተስፋዬ – ፋና)
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን ሁኔታ የሚመረምር ቡድን ወደ ባህርዳር መላኩን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለፀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚያብሄር እንደገለፁት፥ የተላኩት የኮሚሽኑ መርማሪ ባለሙያዎች የተፈናቀሉ ዜጎችን ጨምሮ የሚመለከታቸውን አካላት በማነጋገር የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀም አለመፈፀሙን ያጣራሉ።
የተገኙ መረጃዎችን በማጠናከርም የምርመራ ውጤቱ ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል ብለዋል።
በምርመራ ውጤቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን የሚያመላክት ከሆነም በድርጊቱ የተሳተፉ ግለሰቦችን ተጠያቂ በማድረግ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ ኮሚሽኑ ለምክር ቤቱ ምክረ ሃሳብ አያይዞ እንደሚያቀርብም ተናግረዋል።
በተያያዘም ባለፈው ሳምንት በሰብዓዊ መብት ላይ የተፈጸመን ጥሰት ሲመረምር በነበረ የኮሚሽኑ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኮሚሽነር አቶ ጀማል መሃመድ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ኮሚሽነሩ አውግዝዋል።
በጉዳዩ ላይ አስፈላጊ ማጣራት ተካሂዶ ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረባቸውንም ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።
አቶ ጀማል ላይ ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉት የመንግስት አካላትም ተጠያቂ እንዲሆኑ ኮሚሽኑ እንደሚሰራ ገልጸዋል።
******
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…