ትላንት ሚያዚያ 7/2006ዓ.ም ማለዳ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ በነበረ ፒካ አፕ መኪና ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በሰው ህይወትና አካል ላይ ጉዳት መድረሱን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ገለፀ፡፡
ጽ/ቤቱ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በተሽከርካሪው ላይ ጥቃቱን ያደረሱት ከንጋቱ 12 ሰዓት ተኩል አካባቢ፣ የክልሉ ርዕሰ መዲና ከሆነው ከአሶሳ ከተማ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገ‚ው ሸርቆሌ ወረዳ ልዩ ስሙ ጠይባ ከሚባለው አካባቢ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ በስድስቱ ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
ጥቃቱን ፈፅመው የተሰወሩ ግለሰቦችን አድኖ በህግ ፊት ለማቅረብ የህግ አስከባሪ ኃይሎች ክትትል በማድረግ ላይ መሆናቸውን የገለጸው ጽ/ቤቱ በጥቃቱ ተጠያቂ የሆኑትን ግለሰቦች ማንነት ለማጣራትም ምርመራ መጀመሩን እና የምርመራውን ውጤት የሚመለከቱ መረጃዎችን በወቅቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡
********
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…