አቶ ሙክታር ከድር የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ሆኑ

የጨፌ ኦሮሚያ አራተኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ አቶ ሙክታር ከድርን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር፣ አቶ ለማ መገርሳን አፈጉባኤ አድርጎ በመመምረጥ ተጠናቀቀ፡፡

ጉባኤው በኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ ምክትል ሊቀመንበር በወይዘሮ አስቴር ማሞ የቀረቡትን የአቶ ሙክታር ከድርና የአቶ ለማ መገርሳን ሹመት በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አፅድቋል።

ተሿሚዎቹ የተመረጡት የትምህርት ደረጃቸው የሥራ ታታሪነታቸውና የማስፈፀም ብቃታቸውን ከግምት ውሰጥ በማስገባት ነው ተብሏል።

የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙክታር ከድር እንደገለፁት በምክር ቤቱና በሕዝብ  የተጣለባቸውን ሃላፊነት በብቃት ለመወጣትና የክልሉን ልማትና መልካም አስተዳደር የማስፈን ስራ ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ይሰራሉ።

በሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነትና ብልሹ አሰራር ላይ አቶ አለማየሁ የያዙትን የማይናወጥ አቋም ከዳር ለማድረስና የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

ስር የሰደደውን ድህነትና ኋላቀርነትን ለማስወገድ የገጠርና ከተማውን ሕዝብ በአንድነት ያቀፈ ንቅናቄ በመፍጠር በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሥራ እድል ፈጠራና ሌሎች ተጓዳኝ ዘርፎች ላይ ርብርብ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር በየደረጃው በሚገኙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች በመዘርጋት ውስብስብና ሊፈቱ ያልቻሉ የመልካም  አስተዳደር ተግዳሮቶችን ለማስወገድ የተጀመረውን ፈጣን ልማት እንደሚያስቀጥሉ ገልፀው በንግድ ፣በመሬትና ኢንቨስትመንት፣ በልማት ድርጅቶች የሚታየውን የኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስናን ምንጭ ለማድረቅ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው የክልሉን የሰባት ወራት የሥራ እቅድ አፈፃፀም ሪፓርት፣ሥራ አስፈፃሚዎችን ለማደራጀት የወጣውን አዋጅ ቁጥር 163/2003 ለማሻሻል የተዘጋጀውን ረቂቅ ሰነድ ፣የኦህዴድ ባለሙያዎች ፍቃድ አሰጣጥና የመጋላታ ኦሮሚያን ረቂቅ አዋጅ ጨምሮ የክልሉ ርእሰ መስተዳድርና ዋና አፈጉባኤ፣የኦሮሚያ ሬዲዮና ቲቪ ዋና ሥራ አስኪያጅና ሌሎች ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቋል።

*******
* ምንጭ፡- ኢዜአ፣ መጋቢት 18/2006. 

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago