ምርጫ ቦርድ ሶስት የፖለቲካ ፓርቲዎችን አገደ

(ሰላማዊት ካሳ)

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ደንብን ተላልፈው በመስራት አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ቦርዱ የ 11 ወራት የስራ አፈጻፀም ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበበት ወቅት ነው የፖለቲካ ድርጅቶቹ ህግን ተላልፈው አግኝቻቸውለሁ በሚል ቦርዱ እርምጃ መውሰዱን ያስታወቀው፡፡

በዚህ መሰረትም የኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ( ኦነፓ)፡የኢትዮጵያ ፓን ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢፖኦፓ)፡የኢትዮጵያ ሱማሌ ልማት ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢሱልዴፓ) የታገዱ ሲሆን የሸኮና አካባቢው ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ሾአህድድ) የመጨረሻ ማስጠንቀቅያ እንደተሰጠው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ገልጿል፡፡

የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንደተናገሩት ሶስት አዳድስ የፖለቲካ ፓርቲዎች እውቅና ተሰጥተዋል፡፡አንድ የግንባር እና የውህደት ጥያቄዎችም አዎንታዊ ምላሽ እንዳገኙም ገልጸዋል፡፡

በ2005 በተካሄደው የአካባቢ፣ የአዲስ አበባና የድሬደዋ ከተሞች ምክርቤቶች ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ 48 በመቶ መደርሱም በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡

ቦርዱ ለምርጫው ማስፈጸሚያም ከአራት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ጥቅም ላይ አውሏል፡፡

ከቀረበው ሪፖርት በመነሳትም የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ለነሷቸው የተለያዩ ጥቄዎች ቦርዱ ምላሽ ሰጥል፡፡ በዚህም ቦርዱ በአመቱ ለመስራት አቅዶ ያልተገበረው የዳታ ቤዝ መረጃ አያያዝ ስርአት በአፋጣኝ ሊተገበር እንደሚገባ ምክርቤቱ አሳስቧል፡፡

**********

Source: ERTA – June 28, 2013.

9.14540.489673
Daniel Berhane

Daniel Berhane

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago