በአዲስ አበባ የቀላል ባቡር ግንባታ የተነሳ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት በግዜያዊነት ወደሚቆይበት ብሄራዊ ሙዚየም ዛሬ ሚያዚያ 25/2005 ተዛውሯል፡፡
ሃዉልቱ በነበረበት ቦታ የመሬት ዉስጥ የባቡር መስመር ይዘረጋል፡፡
የአዲስ አበባ የቀላል ባቡር ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር በሃይሉ ስንታየሁ እንዳሉት ሀዉልቱ አስካሁን በነበረበት መሬት ዉስጥ እስከ 20 ሜትር ጥልቀት በመቆፈር ስራዉ ይከናወናል፡፡
የዉስጥ ለዉስጥ ስራው እስከ መጭው ክረምት አጋማሽ ድረስ ተጠናቆ አፈር ይመለስበታል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን በበኩሉ ስራው በተባለው ግዜ ሲጠናቀቅ የአደባባዩንና የመንገዱን ስራ በአዲስ መልክ በመገንባት ሃዉልቱ ወደ ነበረበት ቦታ በቀጣዩ አመት እንዲመለስ ይደረጋል ብሏል፡፡
ሀውልቱ በግዜያዊነት ሲነሳም ሆነ ወደፊት ወደቀድሞ ቦታው ሲመለስ ዉበቱን ከመጨመርና እስካሁን የተጎዱ የሀውልቱን ክፍሎች ከመጠገን ውጭ ምንም አይነት የቅርፅም ሆነ የይዘት ለዉጥ አይደረግበትም::
ሪፖርተር፤ በዛብህ ታደለ
*************
Source: ERTA – May 2, 2013. Originally titled “የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ወደ ብሄራዊ ሙዚየም ተዛወረ”
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…