ፓርቲዎች የተመደበላቸውን ሚዲያ በሚገባ አልተጠቀሙም | Fana

ለአንድ ወር ያህል በተካሄደው የምረጡኝ የመገናኛ ብዙኃን ቅስቀሳ ፣ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አጋር ድርጅቶች በተመደበላቸው የአየር ሰዓትና አምድ ሙሉ ለሙሉ አለመጠቀማቸው ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ልዑል ገብረ እንደተናገሩት፤ በምርጫው የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን ነጻ የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ ተድልድሎላቸው የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን ሲያካሂዱ ቢቆዩም ሙሉ ለሙሉ አልተጠቀሙበትም።

የአየር ሰዓት ድልድሉ ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በተዘጋጀው መመሪያ መሠረት የተከፋፈለ ሲሆን፤በዚህም ኢህአዴግ ከተመደበለት ሰዓት 70 በመቶ ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች 50 በመቶ እንዲሁም አጋር ድርጅቶች 36 በመቶ ተጠቅመዋል ።

«ለምርጫ ዘመቻው የተመደበው የአየር ሰዓት ወደ ብር ሲመነዘር ወደ 12 ሚሊዮን ብር ያወጣል» ያሉት አቶ ልዑል፤የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመደበላቸውን የአየር ሰዓት በአግባቡ አለመጠቀማቸው እንደ ድክመት እንደሚታይ አብራርተዋል።

ይሁን እንጅ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቦርድ እና የብሮድካስት ባለስልጣን ያወጡትን የምርጫ ቅስቀሳ ህግ በአግባቡ መተግበራቸው በስኬት እንደሚጠቀስ ተናግረዋል።

በመጨረሻም መገናኛ ብዙኃን ለቅስቀሳው መሳካት እና ለፖለቲካ ፓርቲዎች ላደረጉት ትብብር ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘገባ ያመለክታል።

በሕጉ መሰረትም የምርጫ ቅስቀሳው ለአንድ ወር መካሄዱ ይታወሳል።

**********

Source: Fana – April 14, 2013. “ፓርቲዎች የተመደበላቸውን አምድና የአየር ሰዓት በሚገባ አልተጠቀሙም“

00
Daniel Berhane

Daniel Berhane

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago