[Trouble reading: Download the article in PDF|169 kb ]
መንደርደሪያ
ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ሰሞኑን ‹‹በኤርትራና በትግራይ ይኖሩ የነበሩ የኤርትራና የትግራይ ዜጐች ተግተው ኢጣልያንን ቢወጉ ኖሮ ከሐረር፣ ከሀድያና፣ ከሲዳሞ፣ ከሸዋ… ወደ
ያም ሆነ ይህ የሰውየው ንግግር ለአፍታ ወደ ታሪክ ማህደር መመለስን ግድ ብሏል፡፡ በመሆኑም ለመንደርደሪያ ይህን በየካቲት 2000 ዓ.ም. ተጽፎ ነገር ግን ‹‹አዲሰ ነገር›› ጋዜጣ ሊያትመው ያልፈቀደው እናም ሳይታተም የቆየ ጽሁፍ ላካፍላችሁ፡፡
ጋዜጣው ለማተም ያልፈቀደበት ምክንያት ምንም ሚስጥር የለውም፡፡ ጋዜጣው ይህን ጽሁፍ ጥሎ ሲያበቃ ከጥቂት ወራት በኋላ ያተመው የፕ/ር መሳይ ከበደን ‘the underside of the Eritrean Issue’ የተሰኘ ጽሁፍ ነበር፡፡ ትኩረት የሚስበው የመሳይ ከበደ ጽሁፍ በጭብጥ የዚህ ጽሁፍ ተጻራሪ እና የመረጃ ፋይዳው አናሳ መሆኑ ብቻ ሳይሆን የአዲስ ነገር አዘጋጆች የመሳይ ከበደን ጽሁፍ ከ12 ወራት በፊት ከታተመበት ከኢትዮ-ሚዲያ ዌብሳይት ወስደው ወደ አማርኛ ተርጉመው ማተማቸው ነው፡፡ በነገራችን ላይ የመሳይ ከበደ ጽሁፍ ጭብጥ ‹‹ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳይያስ አፈወርቂ የኢትዮጲያ አንድነት በጥብቅ የሚደግፍ መሆኑን እና የትግራይ ኤሊቶች ደግሞ ኤርትራውያን ፖለቲካና ኢኮኖሚ እንዳይቀናቀኗቸው ሲሉ የኤርትራን መገንጠል እንደሚፈልጉት ›› ማሳመን ነው፡፡ የዚህ ወቅታዊ አንድምታ የጽንፈኛ ተቃዋሚዎችን ከኤርትራ መንግስት ጋር መሞዳሞድ ምክንያታዊ ለማድረግ ሲሆን በታሪካዊ ገጽታው ደግሞ የትግርኛ ተናጋሪዎች መለያየት የራሳቸው/በተለይም የትግራይ/ ጥፋት ነው የሚል ሀሳብ ነው፡፡
አሁን ፕሮፌሰሩ መስፍን በግልጽ አስቀምጠውታል፡፡
እንዲያውም ‹‹ በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው ከተባለ ለማን አሳፋሪ እንደሚሆን ግልጽ ነው›› ሲሉም ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ ድሮውንም ያለፈ ታሪክ ለምን ይወራል ሲሉ የነበሩት እሳቸውና ተከታዮቻቸው ናቸው፡፡ ሀሳባቸውን ከቀየሩም መልካም፡፡ የቀኝ አክራሪው ክፍል ፊታውራሪ ናቸውና – እንደሳቸው ሚሊዮኖችን በጅምላ መኮነን ሳያስፈልግ – ጥሬ ሀቆችንና የታሪክ ሰነዶችን በተከታታይ በዚህ ብሎግ ላይ በማቅረብ መልስ መስጠት ግድ ይላል፡፡
አሁን ወደጽሁፉ፡፡
[Trouble reading: Download the article in PDF|169 kb ]
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…