​የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ ዴሞክራሲ ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አካሄደ

(አብዱረዛቅ ካፊ)

ከታህሳስ15 እሰከ ዛሬ ታህሳስ 19/2010ዓ.ም የተለያዩ ርዕስ-ጉዳዮችን ሲገመገም የነበረውን የኢሶህዴፓ (የኢትዮጲያ-ሶማሌ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ) ማዕከላዊ ኮሚቴ  መደበኛ ስብሰባ ከሰዓት በኋላ ተጠናቀቀ።

ስብሰባውን የመሩት የኢሶህዴፓ ሊቃመንበርና የክልሉ ም/ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ መሀመድ ኢሳቅና የኢሶህዴፓ ም/ሊቀመንበርና  የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ መሀሙድ ኡመር ሲሆኑ፤ በጉባኤው ላይ ከነበሩት አጀንዳዎች መካካል በ2010ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም በተላይ በውሃ፣ በእንስሳት መኖ፣ በግብርና፣ በትምህርትና በጤና መስክ እቅድ አፈጻጸም፣ በውሀ ዝርጋታና በጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች የተሰሩ ሥራዎች፣ በክልሉ ዞኖችን ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን የሚያስተሳሰሩ መንገዶችና ድልድዮች የተከናወኑ ስራዎች፣ በመልካም አስተዳደርና ፍትህ ስራዎችና በጸጥታ ዘርፍ በተለይም በምዕራብ ሐረርጌ የተጨፈጨፉ ዜጎች ሪፖርት እና ለኢትዮጵያ ሶማሌ ተፈናቃይ ወገኖች የተደረገላቸው ድጋፍና ለወደፊትም ለሚደረግላቸው ድጋፍና የመልሶ ማቋቋም፣ እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጭ አገርም የተሰሩ የድርጅትና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን በጥልቀት ተገምግሟል።

በማዕከላዊ ኮሚቴው ስብሰባ መክፈቻ ላይ የክልሉ ም/ፕሬዚዳንትና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አብዲሀኪም ኢጋል ኡመር በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሐረርጌ የተጨፈጨፉት የሶማሌ ብሔር ተወላጅ ወገኖች ላይ እንደ ክልል መንግስትና እንደ ድርጅትም የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት አቅርበዋል።

በተጨማሪም ም/ፕሬዝዳንቱ የሶማሌ ተፈናቃይ ወገኖች መልሶ ማቋቋም ኮሚቴ ሊቀመንበር እንደመሆናቸው፤ በምዕራብ ሐረርጌ የተጨፈጨፉት የሶማሌ ብሔር ተወላጅ ወገኖች በተመለከተ በፌዴራል መንግስቱ የተሰራውን ስራ በሪፖርታቸው ውስጥ አካትተው አቅርበዋል። ለተፈናቃይ ወገኖች የተደረግላቸውን ድጋፍና ለቀጣይም የሚደረግላቸውን የመልሶ ማቋቋም እቅድም ለኮሚቴው አቅርበዋል።

Logo – Ethiopian Somali People Democratic Party (ESPDP)

በሌላ በኩል የክልሉ ም/ፕሬዝዳንትና የግብናና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሱአድ አህመድ ፋራህ የህዝብ ኑሮ ለማሻሻል የታቀደውና በውሃ፤ በእንስሳት መኖ፤ በግብርና፤ በትምህርትና በጤና መስኮች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቀርበዋል።
በተመሳሳይም የኢሶህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ ኡመር መሀሙድ  በሀገር ውስጥና በውጭ አገርም የተሰሩ የድርጅትና ህዝብ ግኙነት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለኮሚቴው አቀርበዋል።

ከበርካታ ውይይቶችና ግምግማዎች በኋላ ማዕከላዊ ኮሚቴው በልማትና በጸጥታ ዘርፍ በተላይም በንጹህ መጠጥ ዉሃ፣ በመንገዶችና ትላልቅ ድልድዮች፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በወጣቶች ስራ እድል፣ በድርጅት ጉዳዮችና እንዲሁም በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽንና በመልካም አስተዳደር የተሰሩ ሥራዎች አመርቂ መሆናቸውን አስምሮበታል። በተጨማሪም ማዕከላዊ ኮሚቴው የ2010ዓ.ም. የመንግስትና የፓርቲ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

በሌላ በኩል በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ለዘመናት የኖሩት በንጹሃን የሶማሌ ብሔር ተወላጆች ላይ የተፈፀመውን የጅምላ ጨፍጨፋ ድርጊት አውግዟል። በተጨማሪም ለሟች ቤተሰቦችና ዘመድ አዝማድ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልዕክት አስተላለፏል።

በመጨረሻም ማዕካላዊ ኮሚቴው የ2010 እቅድ አፈጻጸም በመገምገም ለተገልጋዩ ህዝብ ስራዎች መጠናከር እንዳለበት፣ የሰላምና ጸጥታ በተለይም በኢትዮጵያሶማሌና ኦሮሚያ ክልል ወሰን አከባቢ ግጭቶችን ማስቆምና ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ሰፊ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው እንደቀጣይ ልማት አቅጣጫዎች አስቀጧል። በተጨማሪም ድርጅቱ ከምን ግዜም በላይ ሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ለማቀራረብና ለማስታረቅ እንደሚሰራ ገልጿል።

********

Guest Author

Guest Author

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago