የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ግዛቸው ሽፍራው የአንድነት አባለት ለፓርቲው ህልውና ሲሉ የተፈጠረውን ችግር በሰከነ መንፈስ እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ::
የፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት በእነ አቶ በላይ ፈቃዱ በሚመራው ቡድን ምክትል ፕሬዝዳንት ግርማ ሰይፉ በኩል ከፓርቲው መሪነት የተነሱት ፓርቲውን የመምራት እና ጫናን የመቋቋም አቅም ስላልቻሉ ነው መባላቸውን በታህሳሱ ምርጫ ፕሬዝዳንታዊ ውድድር አቶ ግርማን በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት ማሸናፋቸውን በማንሳት ኃሳቡን አጣጥለውታል።
በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ቀን ተሸናፊው አቶ ግርማ ራሴን ያየሁበት ውድድር ነው።
ውጤቱም እንኳንስ ፓርቲ ወረዳ መምራት የማልችል መሆኔን የሚያሳይ ነው ማለታቸውን ያስታወሱት ኢንጅነር ግዛቸው ስልጣኔን ያስረከብኩት ፓርቲው በቡድን ፓለቲካ እንዳይፈርስ ለህልውናው በማሰብ ነው ብለዋል።
አሁን ፓርቲውን እያመሰው ያለው የቡድን እና ዝምድና ፓለቲካ ነው የሚል አስተያየት የሰነዘሩት ኢንጅነር ግዛቸው የፓርቲው አባላትም የአንድነትን የቀደመውን ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመፍታት ስልት ተጠቅመው በሰከነ መንፈስ ችግራቸውን መፍታት የፓርቲውን ህልውና እንዲታደጉት ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት የከፈሉት አመራሮች ችግራቸውን በጋራ በውይይት እንዲፈቱ የሁለት ሳምንት ግዜ መስጠቱ ይታወሳል።
*********
ምንጭ፡- ፋና፣ ጥር 09-2007
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…