የቻይና ኤግዚም ባንክ ለመቐለ ወልዲያ ባቡር ፕሮጀክት ብድር ሊለቅ ነው

(ዮሐንስ አንበርብር)

የቻይና ኤክስፖርትና ኢምፖርት (ኤግዚም) ባንክ ለመቐለ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት 1.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ሊለቅ ነው፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሚኒስቴሩ ከፍተኛ ኃላፊዎችና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጌታቸው በትሩ የተገኙበት ቡድን በቅርቡ ወደ ቻይና ሄዶ ባንኩ ባስጠናው የአዋጭነት ጥናት ላይ ማብራርያ አቅርበዋል፡፡

የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት በኢትዮጵያ በኩል ከዚህ ቀደም የተጠና ቢሆንም፣ የቻይናው ኤግዚም ባንክ በድጋሚ ኩባንያ ቀጥሮ የአዋጭነት ጥናት አስጠንቷል፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያትም የቻይና መንግሥት በኢትዮጵያ የፖታሽ ማዕድንን ከማልማት ረገድ ይህ የባቡር ትራንስፖርት መስመር የሚኖረውን ጠቀሜታ አስረግጦ ለመረዳት እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

በዚህም መሠረት በጥናቱ ላይ ለተነሱ ውስን ጥያቄዎች ማብራርያ እንደተሰጠና በቅርቡም ገንዘቡ ይለቀቃል ተብሎ እንደሚገመት ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

የመቐለ ወልዲያ ፕሮጀክት 268.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ለፕሮጀክቱ ብድር ለማቅረብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር መግባባታቸው ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እያደረጋቸው የሚገኙ ሦስት የባቡር ፕሮጀክቶች ማለትም የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር፣ የአዲስ አበባ ሜኤሶና የሜኤሶ ድሬዳዋ ደወሌ የባቡር ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ ከቻይና በተገኘ ብድር በመገንባት ላይ ይገኛሉ፡፡

ብቸኛው ከቻይና ውጪ በተገኘ ብድር ለመገንባት ዝግጁ የሆነው ፕሮጀክት የአዋሽ ወልዲያ የባቡር መስመር ሲሆን የሚገነባው ከአውሮፓ ባንኮች በተገኘ ብድር ነው፡፡ ይህም መስመር በቻይና ብድር ከሚገነባው የመቐለ ወልዲያ ፕሮጀክት ጋር የሚገናኝ ነው፡፡

********

ምንጭ፡- ሪፖርተር፣ ሕዳር 21-2007

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago