የኢህአዴግ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን ጷጉሜ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ጀመረ፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድና ከ2006 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ጋር በማያያዝ የመንግስትና የድርጅት ሁኔታን መገምገም ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ በግምገማው ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ለውጥ በማምጣት ረገድ የተደረሰበትን ደረጃ በዝርዝር መመልከት መጀመሩን የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ለኢትተጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
የኢህአዴግ ምክር ቤት የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚን በልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ በመቀየር ሂደት ውስጥ በታዩ ጥንካሬዎችና ድክመቶች ላይም ረትኩረት ሰጥቶ መገምገም መጀመሩን በመግለጫው ተመልክቷል፡፡
በዚህ ረገድ ባለፉት 13 ዓመታት የተከናወኑ ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ተግባራትን ተከትሎ የልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ ደረጃ በደረጃ እየጎለበተ የመጣ ቢሆንም ከሚፈለገው ፍጥነት አኳያ ብዙ የሚቀረው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በየደረጃው የሚገኘው አመራር በተለይም ከፍተኛ አመራሩ የነበረውን ሚና ምክር ቤቱ በዝርዝር መመልከት መጀመሩን ነው በመግለጫው የተብራራው፡፡
የኢህአዴግ ምክር ቤት ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት ረገድ ባለፉት አራት ዓመታት የተፈጸሙ ተግባራትን በመገምገም የርብርብ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ አንዱ መሆኑ መግለጫው አመልክቷል፡፡
ምክር ቤቱ ከዚህ በተጨማሪ ሁሉንም የልማት አቅሞች አንቀሳቅሶ በመምራት የልማት ሠራዊት በመገንባት ረገድ የተገኙ ስኬቶችና እጥረቶችን ለመለየትና በሌሎች ጉዳዮች ላይም ግምገማውን ቀጥሏል ብሏል መግለጫው፡፡
የምክር ቤቱ ስብሰባ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ከላከው መግለጫ ለመረዳት ተችሏል፡፡
********
ምንጭ፡- ኢቢሲ፣ ጳጉሜን 3/2006.
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…