(መሓሪ ይፍጠር [email protected]m)
(ክፍል ሁለትና የመጨረሻው)
ውድ አንባቢያን በክፍል አንድ ፅሑፌ ላይ “ጆቤ” በሰራዊቱ ግንባታ ሰነድ ላይ ያነሷቸውን ሃሳቦች ከተጨባጭ ሰነዱ ጋር በማመሳከር ነጥቦቹ ትክክል አለመሆናቸውን ለማሳየት ሞክሬያለሁ። ሰውዬው ለማንሳት የሞከሯቸው ሌሎች ጉዳዩችንም እንዲህ ተመልክቻቸዋለሁ። መልካም ንባብ።…
ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል ሰነዱን አስመልክተው ያነሷቸው ሃሳቦች ለእርሳቸው ፍጆታ በሚውል መልኩ ቀነጫጭበውና እውነት አስመስለው ለማቅረብ ሞክረዋል። ለዚህም “በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓታችን ደህንነት መከላከል ማለትና የሀገር ደህንነት መከላከል ማለት በመሰረቱ አንድ ነው ማለት ይቻላል” የሚለውን አባባል ለማብራራት የተቀመጡትን ሃሳቦች ሆን ብለው ለመመልከት አልፈቀዱም ወይም አይተው እንዳላዩ አልፈዋቸዋል። ይሁንና እኔ ግን ሃቁን ለመግለፅ እሞክራለሁ። በማንኛውም ሀገር ውስጥ ሀገርን በመምራት ላይ የሚገኝ ኃይልን በታጠቀ ኃይል የመቀየር ተቃውሞ በሚያጋጥምበት ወቅት፤ ስርዓቱ ምንም ዓይነት ይሁን (ፊውዳላዊም ሆነ አብዮታዊ፣ ሊበራላዊ ሆነ ሃይማኖታዊ…ወዘተ) ሌላ ጉዳይ ሆኖ፣ ያ ስርዓት ደህንነቱን ለማስጠበቅ ሲል የመከላከያ ኃይሉን ተጠቅሞ ራሱን መከላከሉ የሚቀር አይሆንም። ይህ ደግሞ ከፓርቲው ውጪ ሆኖ አንድን ፓርቲ አሊያም ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ከመጠበቅ አንፃር ሊገለፅ እንደሚችልና ይህም የሀገርን ደህንነት መጠበቅ ማለት እንደሆነ መፅሐፉ ያስረዳል። እናስ ጡረተኛው ጄኔራል መኮንን ከቶ ምን እያሉን ይሆን?
ያም ሆነ ይህ ግን በቅድሚያ በመፅሐፉ ላይ የተጠቀሰው “በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ…” የሚለው አባባል ከሀገራችን ነባራዊ ታሪክ እንዲሁም ፖለቲካል ኢኮኖሚ ሁኔታ አኳያ የተሳሰረ መሆኑን ግለሰቡ የሚዘነጉት አይመስለኝም። ይህ ማለት ደግሞ ባለፉት 25 ዓመታት በተከናወኑት አምስት ሀገራዊ ምርጫዎች መራጩ ህዝብ እዚህ ሀገር ውስጥ የአውራ ፓርቲ ስርዓት (Dominant Party System) እውን እንዲሆን ይሁንታውን ሰጥቷል። እንደሚታወቀው በአንድ ሀገር ውስጥ የአውራ ፓርቲ ስርዓት አለ የሚባለው፤ ገዥው ፓርቲ ለብቻው ወይም በጥምረት (ተጣማሪው ፓርቲ ተመሳሳይ ፖሊሲን የሚከተል ከሆነ) ለረጅም ጊዜ መንግስት ሆኖ የመሪነቱን ቦታ ሲይዝ ነው።
ይህ የፖለቲካ ስርዓት ዓይነት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት አካሄድን የሚከተል በመሆኑም፤ በውስጡ ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በህጋዊ መንገድ ተንቀሳቅሰውና ሃሳባቸውን በግልፅ አስረድተው በሀገሪቱ ውስጥ በሚደረጉ ምርጫዎች ተወዳድረው የማሸነፍ ህጋዊ መብት አላቸው። ስርዓቱን ከሚያራምዱ ሀገሮች ውስጥ ጥቂቱን በማሳያ ምሳሌነት ብናነሳ እንኳን፤ የናይጄሪያን፣ የሩዋንዳን፣ የኢኮቶሪያል ጊኒን፣ የደቡብ አፍሪካንና የጃፓንን አውራ ፓርቲዎች መጥቀስ የሚቻል ይመስለኛል። ይህም የአውራ ፓርቲ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በዓለም ላይ ያለና በርካታ ሀገራት የሚከተሉት መሆኑን ያሳያል። የሀገራችንም የአውራ ፓርቲ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ከዚሁ ነባራዊ ሁኔታ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።
እናም በእኔ እምነት ይህ የአውራ ፓርቲ ስርዓት በህዝቡ ምርጫ እውን የሆነበት ተጨባጭ ምክንያት፤ የህዝቡን ቀልብ መሳብ የቻለ ወይም ለአቅመ-ተቃዋሚነት የደረሰ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው። በሌላ አገላለፅ ህዝቡ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱ ያመጣውን የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታን አካሄድን መተኪያ በሌለው አማራጭነት መቀበሉና ተቃዋሚዎችም ለይስሙላ በህገ መንግስቱ እየማሉ፣ በሌላ በኩል ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ በመሞከራቸው በእነርሱ እምነት ማጣቱን የሚያሳይ ነው። እናም እንዲህ ዓይነቱ ተጨባጭ የህዝብ ፍላጎት ባለበት ሀገር ውስጥ፤ የሀገሪቱ ዘብ የሆነው የመከላከያ ኃይል ከገዥው ፓርቲ ርዕዩተ-ዓለም ተነጥሎ እንደምን ሊገነባ እንደሚችል የሚያውቁት እርሳቸው ብቻ ይመስሉኛል።
ምንም እንኳን እርሳቸው ”የምንገነባው መከላከያ ኃይል አላማው የስርአታችንን ደህንነት መጠበቅ ነው ሲባል የሚገነባውና የሚመራው በስርአቱ መሪ የሆነው አካል ብቻ ነው” የሚለውን የመፅሐፉን አባባል በሚያስገርም ሁኔታ “በጭንቀት፣ በልመና የተደጋገመ ጸሎት አይሉት ምህላ…” በማለት ሰራዊቱ የሚገነባው ለጥቂት ግለሰቦች ጥቅም ሲባል እንደሆነ አስመስለው ለመግለፅ ቢሞክሩም፤ ሃቁ ግን አሁንም በመፅሐፉ ላይ የተጠቀሰውን ማብራሪያ ሆን ብለው በመዝለል እርሳቸው ካላቸው ፍላጎት በመነሳት ያልተገባ ስያሜ ለሰራዊቱ ለመስጠት ያለመ ይመስለኛል። አዎ! “ጆቤ” ከጠቀሱት አባባል በታች ሰነዱ ገፅ 28 ላይ፤ የመከላከያ ኃይሉን የመምራት፣ የመገንባትና የማሰማራት ሁኔታዎችን ከማንም ጋር በመከፋፈል ሊከናወን እንደማይችልና እንዲህ ዓይነቱ አሰራር በሌሎች ስርዓቶችም ገቢራዊ እንደሚሆን ያብራራል። አንድ በስልጣን ላይ የሚገኝ አካል መሪነቱን ከሌሎች ጋር የማይጋራበት ወይም የማይከፋፈልበት ሁኔታዎችና አጋጣሚዎች ብዙ ቢሆኑም፣ ወትሮና በማንኛውም ጊዜ የአመራሩን ጉዳይ በተመለከተ ወደ ድርድር የማያቀርበው ነገር ቢኖር የስርዓቱን የመጨረሻ ምሽግ የሆነውን የመከላከያ ኃይል እንደሆነ መፅሐፉ በግልፅ ያስረዳል።
እርግጥም ሌላው ቀርቶ አድጋለች በምትባለው አሜሪካ ውስጥም ቢሆን የሚገነባ ሰራዊት እንኳን ሳይቀር የሊብራሊዝም ቀኖናን ከልጅነቱ ጀምሮ በተረትና ምሳሌ መፅሐፎች ላይ ሳይቀር እየተነገረውና እየተማረ ያደገ መሆኑን “ጆቤ” የሚስቱት አይመስለኝም። ካደገም በኋላ ቢሆን ሰራዊት ውስጥ ገብቶ “መኮንን” (officer) መሆን የሚችለው ለስርዓቱ ካለው ቀረቤታና ታማኝነት አኳያ እየተመዘነ ነው። ይህ ካልሆነና ግለሰቡ በስርዓቱ ላይ በቂ እውቀት ከሌለው ከ“ባለ ሌላ ማዕረግተኞች” (Non-Commissioned Officers /NCO’s/) ምድብ ይሆንና ወሳኝ በሆኑ የመሪነት ጉዳዩች ውስጥ እንዳይገባ ይደረጋል። ሊብራል ስርዓቱን የሚቃወም ከሆነ ደግሞ፤ ወደ ሰራዊቱ ሊቀላቀል አይችልም። እናስ ለጡረተኛው ሜ/ጄኔራል የእኛ ሀገሩ ሁኔታ አዲስ መስሎ የታያቸው ከምን መነሻ በመነጨ ይሆን?—በእኔ እምነት እንዲያው ዝም ብለው በደፈናው የሰራዊቱን የግንባታ መስመር በማጣጣል ጥላሸት ለመቀባት አስበው ይመስለኛል።
እርግጥም ይህ የእርሳቸው ጥላሸት የመቀባት ፍላጎት “መጽሐፉ ሕገ-መንግስታችንን በውል መጥቀስ የጀመረው በገጽ 87 ነው” እስከሚለው የቅጥፈት ድርሰታቸው ድረስ የሚዘልቅ ነው። ለነገሩ ማንም ሰው ያንን መፅሐፍ ገለጥ ቢያደርገው ሩቅ ሳይሄድ በገፅ 23 ላይ ህገ መንግስቱን ቢያንስ ሁለቴ ተጠቅሶ ያገኘዋል። እናም እኔ ‘ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል ሆይ! ለምን ይዋሻል?’ ብዬ ልጠይቃቸው እወዳለሁ—እውን የሰራዊቱን ህገ መንግስታዊ ፅናት በሐሰት የገፅ ቁጥርን በመቀያየር ጭምር ኢ-ህገ መንግስታዊ ማድረግ ይቻላልን?—መቼም “ጆቤ” የህግ ምሁር እንደመሆናቸው መጠን፤ እንበልና አንድ ሰው እንዲከሰስ የሚመለከተው አንቀፅ ቁጥር 23 ሆኖ ሳለ፣ በአንቀፅ ቁጥር 87 ሊወነጀል እንደማይችል ከእኔ በላይ ስለሚያውቁ ስለ ቁጥር ምንነትና መዘበራረቅ ልነግራቸው አልሻም—እንዲህ ዓይነቱን የውሸት የቁጥር ጨዋታን ለምን ለመጫወት እንደሞከሩ የሚያውቁት እርሳቸው ናቸውና።
በዚህ ሁኔታ የሰራዊቱን የግንባታ ሰነድ ቁጥሩን ሳይቀር በሐሰት ያዘበራረቁት “ጆቤ” ዝቅ ብለውም “መዘባረቁን በማያሻማ ሁኔታ እየቀጠለ (ሰነዱን ማለታቸው ነው) ‘ኢህአዴግ ከሌለ ይህች ሀገር የለችም የሚለውን አባባል ሲያመላልሰው ይታያል’ ይሉናል። እኔ ግን እርሳቸው እንዳሉት አይመስለኝም። እናም አባባሉን ግን ከግሌ እምነት በመነሳት ለማብራራት እሞክራለሁ—ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል አውቀው የዘለሉትን የመፅሐፉን ክፍሎች በማጣቀስ ጭምር።
በእኔ እምነት በመንግስት የተዘጋጀው ይህ ሰነድ ትክክል ይመስለኛል። ምክንያቱም ገዥው ፓርቲ ባይኖር ኖሮ፤ የዛሬ 25 ዓመት ገደማ ታጥቀው የነበሩ 17 የሚጠጉ የተለያዩ ብሔር-ተኮር ድርጅቶችን በአግባቡ ማስተናገድ ባልተቻለ ነበር። በወቅቱ ገዥው ፓርቲ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ህግን ተከትሎ ብርቱ ተግባር ባያከናውን ኖሮ፤ አንዳንድ ሟርተኞች “ኢትዮጵያ ትበታተናለች፤ አበቃላት” በማለት የተነበዩት ነገር ዕውን በሆነ ነበር። ምስጋና ለገዥው ፓርቲ ይሁንና ይህ የመበተን አደጋ ተፈፃሚ አልሆነም። የዛሬን አያድርገውና ራሳቸው “ጆቤ”ም ቢሆኑ ስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት (ከዛሬ 15 ዓመታት በፊት ማለቴ ነው) ይህን እውነታ ይጋሩት ነበር—አዲስ ኒዮ-ሊበራላዊ ካባን ተከናንበው ብቅ ካሉበት ከተሃድሶው መስመር በፊት። ታዲያ ምነዋ ዛሬ ላይ ይህን ዕውነታ ከ15 ዓመት በኋላ በተገለበጠ መነፅር ለመመልከት ፈለጉ?—ህገ መንግስቱን ስለተፃረሩ ከኃላፊነታቸው በመነሳታቸው ምክንያት ነው ወይስ በሌላ?—እርግጥ ምላሹ የእርሳቸው እንጂ የእኔ አይደለም።
“ጆቤ” ከመፅሐፉ ለመጥቀስ አልፈለጉም እንጂ ሰነዱ ዕውነታውን በራሱ መንገድ ገልፆታል። ይኸውም ስርዓቱ ከሌለ ህዝቦች ለዘመናት ሲጠይቁ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት ዕውን እያደረጉ ያሉት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የምጣኔ ሃብት ልማት፣ የማህበራዊ ዕድገት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ አንድነትና ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት…ወዘተ የመሳሰሉ ጉዳዩች ሊኖሩ እንደማይችሉ ያትታል። እነዚህ ጉዳዩች ከሌሉ ደግሞ ሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ ተከስቶ ወደ ለየለት ብተና ማምራታችን እንደማይቀርም እንዲሁ።
እርግጥም እዚህ ሀገር ውስጥ የተፈጠሩት የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ እመርታዎች ስርዓቱን የሚመራው ገዥ ፓርቲ በተከተለው ትክክለኛ የዕድገት መስመር የተገኙ ናቸው። ስርዓቱን የሚቃወሙ ወገኖች ካሉ፤ እየተቃወሙ ያሉት ይህን ሁለንተናዊ የዕድገት ጎዳና ነው። ይህ የዕድገት መስመር ከተቋረጠ ደግሞ ከፌዴራላዊ ስርዓቱ አኳያ ገና ጀማሪ የሆንባቸውና ካለፉት ስርዓቶች ሲንከባለሉ የመጡት የገዥና ተገዥ ስንኩል አስተሳሰቦች የተፈጠረውን ዴሞክራሲያዊ አንድነትና ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት በመሸርሸር ሀገራችንን የሁከትና የብጥብጥ አውድማ ማድረጋቸው የሚቀር አይመስለኝም። በቅርቡ በኦሮሚያና በጎንደር አንዳንድ አካባቢዎች የታዩትና ሀገራችን እንድትበተን የሚሹ የውጭ ሃይሎች እንዲሁም የውስጥ ጀሌዎቻቸው አማካኝነት የተቀነባበሩት የፀረ- ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትና የህገ ወጥነት ዝንባሌዎች የዚሁ ሃቅ ጥሩ ማሳያዎች ይመስሉኛል።
እናም በእኔ እምነት ይህን ችግር መፍታት የሚችለው በህገ መንግስቱ መሰረት ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትንና አንድነትን ዕውን ያደረገው እንዲሁም ህዝቦችን አስተባብሮ ዛሬ ለደረስንበት የህዳሴ ጉዞ ያበቃን ገዥው ፓርቲና እርሱ የሚከተለው ርዕዩተ-ዓለም ብቻ እንጂ፣ እነ “ጆቤ” የሚያቀነቅኑለትና ከሀገራችን ታሪክና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አብሮ የማይሄደው እንዲሁም ጥቂቶችን ቱጃር አድርጎ ሚሊዮኖችን በድህነት አረንቋ ውስጥ የዘፈቀው የኒዮ-ሊበራሊዝም ቀኖና አይደለም። ይህ የእኔ እምነት ነው፣ የጡረተኛው ሜ/ጄኔራል አስተሳሰብ ደግሞ ሌላ ሊሆን ይችላል—መብታቸው ነው።
አዎ! ከዛሬ 25 ዓመት በፊት ሀገራችንን ከብተና ያደነ መስመር፤ ዛሬም ሆነ ነገ ከሚጋረጡብን ማናቸውም አደጋዎች የሚያድነን ገዥው ፓርቲ ብቻ መሆኑን አስረግጨ መግለፅ እወዳለሁ። ኧረ ለመሆኑ እውነት…እውነቱን እንነጋገር ከተባለ፤ ኢህአዴግ ባይኖር ኖሮ ከቶ የትኛው ኃይል ነው የዚህን ሀገር ችግር በሰከነ ሁኔታ ተሸክሞ ሊሄድ የሚችለው? የትኛውስ አቅም ያለው ፓርቲ ነው እርሱን ሊተካው የሚችለው?…ለምን ሃቁን እያወቅን “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” እንዲሉት ይትብሃል ዓይነት እንደባበቃለን?…ያም ሆነ ይህ ግን እዚህ ሀገር ውስጥ በመተግበር ላይ ያለውን ስርዓት ያመጣው ገዥው ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን፣ ስርዓቱን የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት መከላከያ ሰራዊቱም ከዚህ አኳያ ዕውነታውን ቢገነዘበው ምንም ዓይነት ችግር ሊኖረው የሚችል አይመስለኝም— እየተነገረ ያለው ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ከፓርቲ ወገንተኝነት ውጪ ስለመጠበቅና ስለ መከላከል ጉዳይ ነውና።
ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል በሰነዱ ላይ “እኛ ብለው የሚፅፉ አመራሮች በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሽፋን እኛን አገልግሉ ከሚል ውጪ፣ ያስቀመጡት የተለየ የግንባታ ዓላማዎችና አቅጣጫዎች የሉም” ይላሉ። ለጥቀውም “እኛ” ማነው? ብለው ይጠይቁና ወረድ ብለው ደግሞ፤ “በሰራዊት ግንባታ ላይ ያለው ‘እኛ’ አድሃሪ ነው፣ ፀረ-ዴሞክራቲክ ነው፣ ፀረ-ህገ መንግስት ነው” የሚል ብያኔ ራሳቸው ላነሱት ጥያቄ ምላሽ ራሳቸው ይሰጣሉ። እንዲህ ዓይነት ክስተት ሲያጋጥም ይመስለኛል የሀገራችን አርሶ አደር “አንቺው ታመጪው፣ አንቺው ታሮጪው” የሚለው። ለመሆኑ “እኛ” ማለት ችግሩ ምንድነው?—እርግጥ “እኛ”ን “ጆቤ” አያውቁትም ብዬ አላስብም። አዎ! መፅሐፉን ያዘጋጀው መንግስት “እኛ” ሲል ጥቂቶችን ሳይሆን በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመር የሚያምነውን ማንኛውንም የህብረተሰብ ክፍል ማለቱ ይመስለኛል—በተለይም የተሃድሶውን መስመር ለማሳለጥ የተሰለፈውንና ከታች እስከ ላይ ያለውን የህብተረሰብ ክፍል። “እነርሱ” ከተባለ ደግሞ ምናልባትም የተሃድሶውን መስመር ለማደናቀፍ የተሰለፉት እነ “ጆቤ” እና ጥቂት የሃሳብ አጋሮቻቸው ሊሆኑ የማይችሉበት ምክንያት ያለ አይመስለኝም። እናም የሰነዱ ባለቤት የሆነው መንግስት “እኛ…እኛ ነን፤ ‘እናንተ’ ደግሞ እናንተ ናችሁ” ሊላቸው ቢችል ምላሻቸው ምን ሊሆን እንደሚችል አላውቅም።
ያም ሆኖ ግን የ“እኛ” እና “የእነርሱን” የቃላትና የተግባር አሰላለፍን እዚህ ላይ ልግታውና ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል “እኛ የሚለው አድሃሪ፣ ፀረ-ዴሞክራቲክና ፀረ-ህገ መንግስት ነው” በማለት ስለገለፁት የተሳሳተ ምልከታ ላምራ። እርግጥ “እኛ” ማለት በዋነኛነት ከተሃድሶው መስመር ወዲህ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመሩን በመከተልና እርሱን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ ለሀገሩ ሁለንተናዊ ዕድገት ደፋ ቀና ብሎ ራሱን በየደረጃው በመጥቀም ሀገሪቱን ያሳደገ አብዛኛው ህዝብ መሆኑን ከተግባባን ዘንዳ፤ ይህ ህዝብና አመራሩ “ጆቤ” እንደሚሉት ከቶም አድሃሪ ሊሆን አይችልም። ይህ ሉዓላዊ ስልጣኑን ተጠቅሞ በህገ መንግስቱ መሰረት አብዮታዊ ዴሞክራሲን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በካርዱ የመረጠ የተሃድሶው መስመር ህዝብ ፀረ-ዴሞክራቲክና ፀረ-ህገ መንግስት ተብሎም ሊፈረጅ አይችልም። እንዲህ ዓይነቱ ጥቅልና ተገቢ ያልሆነ ፍረጃ አንድም እዚህ ሀገር ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ጉዳይ ያለመገንዘብ፣ ሁለትም አመራሩን እንኳን ብንተወው ህዝቡን መናቅ ከፍ ሲል ደግሞ በህገ መንግስቱ ላይ መዘባበት ይመስለኛል። ይህ ሃቅም በእኔ እምነት “እነርሱ” ወደ ሚለውና ተሃድሶውን ለማደናቀፍ ወደ ተሰለፉት ሃይሎች የሚወስደን ይመስለኛል። እነ “ጆቤ”ን ያንጠባጠበው የተሃድሶው ባቡር ለውጥና ዕድገት ፈላጊውን የሀገራችንን ታታሪ ህዝብ አሳፍሮ ተጠቃሽ የሚሆን ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገትን ያስመዘገበ፣ ዴሞክራሲ እንደ ሸቀጥ ከውጭ የሚገባ ቁሳቁስ አለመሆኑን ተገንዝቦ ከሀገሩ ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ ዴሞክራሲውን የቀመረ፣ በሀገር ውስጥ ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በመጠበቅ አስተማማኝ ሰላምን ከመፍጠር ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከበሬታን ያገኘና ለጎረቤቶቹ ጭምር ቤዛ እየሆነ ያለን ሰራዊት የገነባ ህዝብ ነው ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የተሰለፉት እነ “እነርሱ” ናቸው በአድሃሪነት፣ በፀረ-ዴሞክራቲክና በፀረ-ህገ መንግስትነት መፈረጅ የሚኖርባቸው?—መልሱን ለዚህ ፅሑፍ አንባቢ እተወዋለሁ። አንድ ጉዳይ ግን ለመግለጽ ፈለግሁ። የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ገና በመግቢያው ላይ ሲጀምር “እኛ …” ብሎ ነው። ይህ ማለት ደግሞ የሀገሪቱን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እንደሆነ ይጠፋዎታል ብዬ አልገምትም። እናም ሰነዱን በኢ-ህገ መንግስታዊነት እየተቹ መልሰው ራስዎ ህገ መንግስቱን እየተቃረኑ አይመስልዎትምን?
ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል በሰነዱ ላይ ያሉት ጉዳዩች በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይና የደህንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይም የተቀመጡ መሆናቸውን ገልፀዋል። ሆኖም ያ ሰነድ በአደባባይ ለህዝብ ሰራዊቱን “የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ወይም የኢህአዴግ የመጨረሻ መከላከያ ምሽግ ነው አይልም” የሚል የመቃወሚያ ሃሳብ በማንሳት “ለምን?” ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ጥያቄያቸው ሁለት ጉዳዮችን የያዘ ነው። አንደኛው የሰራዊቱ የግንባታ ሰነድ በድብቅ ለሰራዊቱ የተዘጋጀ ማስመሰል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በሀገራዊ ስትራቴጂና በአንድ ተቋም መመሪያ መካከል ያለውን ልዩነት ሆን ብሎ ለማምታታት መፈለግ ነው። ይሁንና “የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚለው ሰነድ በህገ መንግስቱ መሰረት የተዘጋጀና ማንኛውም አካል በቀላሉ ሊያገኘው የሚችል ነው። ለዚህም እኔ ራሴ እማኝ መሆን እችላለሁ። አንድ መከላከያ ውስጥ የማውቀውን ወዳጄን ‘መፅሐፉን ማንበብ ስለምፈልግ ወታደራዊ ምስጢር ከሌለበት አምጣልኝ’ ብዬ ስጠይቀው ሰነዱን እጄ ላይ ለማስገባት የሁለት ሰዓት ጊዜ እንኳን አልፈጀብኝም። እርግጥም መፅሐፉ የተደበቀ ነገር የሌለው በመሆኑ በእጅ ለማስገባት ይህን ያህል ቀላል ነው።
ፖሊሲንና ስትራቴጂን ከአንድን መንግስታዊ ተቋም መመሪያ ጋር ሆን ብሎ ለማጣረስ በጡረተኛው ጄኔራል መኮንን የተደረገው ጥረትም ግርምትን ያጭራል። እርግጥ እርሳቸው ስለ ስትራቴጂና መመሪያ ዕውቀት የላቸውም ባልልም፤ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንድን ዓላማ ለማሳካት ስለ አጠቃላይ ጉዳይ ምስል የማስያዝና በአጠቃላዩ ውስጥ ያሉት ክፍልፋዩች የተተለመውን ዓላማ ለማሳከት እንዴት እንደሚዛመዱ የሚያሳይ ጥቅል አቀራረብ ነው። በተለይም ስትራቴጂ በማንኛውም ጊዜ የሚቀየር አይደለም። ለስትራቴጂው መነሻ የሆኑት ጉዳዩች ወይም የስትራቴጂው ዓላማዎች ሲቀየሩ ስትራቴጂውም አብሮ ይለወጣል። የውጭ ጉዳይና የደህንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይም ከዚሁ አኳያ የመከላከያ ጉዳዩች በጥቅል በተቀመጡ ሃሳቦች ተገልፀዋል። ይህ ማለት ግን ተቋሙ በመመሪያነት የሚያወጣቸው ዝርዝር ጉዳዩችን ፖሊሲውና ስትራቴጂው ይመለከተዋል ማለት አይደለም። እናም በሰነዱ ላይ ስለ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ባይገለፅም፤ መንግስት በተቋሙ ዝርዝር አሰራር ውስጥ እንዲሰፍር ማድረጉ ተገቢ ይመስለኛል። ጥቅል ጉዳዩችን በሚይዘው ፖሊሲና ስትራቴጂ ውስጥ ሁሉንም ነገር ዘርዝሮ ማስገባት አይቻልምና።
“ጆቤ” በሚያስገርም ሁኔታ “ከህገ መንግስቱ ጋር ይጋጫል” በማለት ያልተገባ ስም ሰጥተውት “ከስራ ይታገድ” የሚል “ብይን” እንደ ዳኛ ያስተላለፉበት ሰነድ፤ እርሳቸው ያልጠቀሷቸውን የሰራዊቱን ወታደራዊ ግንባታ እጅግ በሚበዙት ገፆቹ ይተነትናል። ከእዚህ መካከል መፅሐፉ ጦርነት የፖለቲካ አንድ ገፅታና ተቀጥያ መሆኑን፣ ስለ መከላከያ አቅም በተለይም ስለ ጦርነት አቅሞች ምንነት፣ ኢኮኖሚ የመከላከያን አቅም ለማጠናከር ወሳኝ ጉዳይ ስለመሆኑ፣ ስለ ወታደራዊ ግንባታ ምንነት፣ መነሻና አፈፃፀም እንዲሁም በአነስተኛ ወጪ ጠንካራ የመከላከያ አቅምን ስለመገንባት ብሎም በመከላከያ ግንባታና በኢኮኖሚ ልማት መካከል ስላለው መደጋገፍ ከወቅቱ የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ ጋር እያስተሳሰረ በሳይንሳዊ መንገድ የሚተነትን ነው። እናም ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል “ከስራ ይወገድ” ያሉት ሰነድ እነዚህን ወታደራዊ ሳይንሳዊ ትንታኔዎችን ጭምር የያዘ ነው። እርግጥ ሰውዬው ምን እያሉን ነው?…አንድ ስለ “ደርግ መጣ” አስተያየት የሚሰጥ ሰው፤ ማንኛውንም ነገር “ይወገድ” የሚል ከሆነስ ራሱ ስለ ደርግነት ማቀንቀን አይሆንበትምን?
በመጨረሻም ጡረተኛው ሜ/ጄኔራል “ከስራ ይወገድ” በማለት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅፈው በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ያደረጉት የሰራዊቱ የግንባታ ሰነድን የተመለከተው ደብዳቤያቸው በግብዓትነት የሚያገለግል ይመስለኛል። ግብዓትነቱ ግን ደብዳቤው እንደሚለው ሰነዱ ከህገ መንግስቱ ጋር በመጋጨቱ ዳግም እንዲታይ አይደለም—ቀደም ሲል ባቀረብኳቸው ተጨባጭ ማስረጃዎች ሰነዱ ህገ መንግስቱን የሚደግፍ እንጂ የሚቃረን አይደለምና። እናም ግብዓትነቱ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እርሳቸው ለሚመሩት ድርጅትና ሀገር ጭምር ነው። ይኸውም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ ለመገናኛ ብዙሃን ለተሃድሶው መስመር እንቅፋት የሆኑ ጉዳዩችን ለመለየት ድርጅታቸው ሰፊ ውይይት ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለገለፁበት አግባብ፤ የተሃድሶው መስመር ያንጠባጠባቸው ወገኖችም የተገኘውን አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም ሳይታክቱ በሚዲያ የሚለቋቸው አደናጋሪና ጥላሸት ቀቢ ፅሑፎች እስከ የት ድረስ ሊጓዙ እንደሚችሉ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳያቸው ይመስለኛል።
**********
Mr. Tahir Kedir (Tahir Hawes of somalia),
I think you are one of the ill politicians those who are tired of trying to destabilize our beloved country Ethiopia.
I’m saying this because;
When you are listing the companies owned by the Tigrians I tried to identify who the owners are and when I know the truth I was laughing at you. Any ways the truth is,
Of the ≥6 cement factories it is only one (Mesebo cement) owned by Tigrians,
Of the ≥4 car assembling factories it is only one (Mesfin Industry) owned by Tigrians,
Of the 16 private Banking it is Only one owned by Tigrians
All the Regional states and most of the ethnic groups have their own development associations,
There is no beverage factory in Tigray except Raya beer(but there are about 20 beverage factories in Ethiopia),
Oh! I’m tired of correcting your feeble lies.
Here in Ethiopia there is space for lie, the time is for hard working people and let me go to my work. To survive everybody has to work hard.
This is the truth.
Please ! send your regular issue . you are my favorite news paper
እስኪ የትግራይ ተወላጅ ሆኖ አዲስ አበባ
ውስጥ እየኖረ ቪላ ባይኖረው
እንኩዋን ኮንዶሚኒየም የሌለው ? I am Tigraway and i lived for more than 30yrs in Addis but i have no villa or condo even if i have been registered 12yrs ago. There are so many Tigraway that have the same story .Generalization is not true.Stop racism !!!
የአፓርታይድ አገዛዝ ለምን ትላላችሁ ለምትሉ
መልስ ይሆን ዘንድ ሼር አድርገናል::
እኔ የምለው
1. ይህ ህዝቡ ያነሳው የመብት ጥያቄ የዘመናት ጥያቄ አይደለምን
….ከዘመናት በሁዋላ “የተደርሰበት ሁኔታ ነው ያለው” ምትሉን መቼ
ነው መፍትሄ ምትሰጡት?
2. የፍትህ ፣ የነፃነት ፣ የእኩልነት ጥያቄ በኢትዮጵያ የለምን?
3. የአንድ ዘር የበላይነት እና ተጠቃሚነትን አላየንምን? (መቸም
ይህንን ለማስረዳት ጉድጉዋድ መቆፈር አይጠበቅብኝም)
4. አገሪቱዋ ተመጣጣኝ የሆነ የሃብት ክፍፍል ይታይባታልን?
ምሳሌ ማንሳት ቢያስፈልግ …ኢትዮጵያ
– አንድ ያላት የወርቅ ማእድንን (ሻኪሶ የሚገኝ) ብሄራዊ ማእድን
ልማትን ጨምሮ በፕራይቬታይዜሽን ስም ለአንድ ግለሰብ የተሰጠባት
– የመሬት ሃብትዋ ስልጣንን እና ዘርን ተገን አድርጎ ያለ አግባብ
የሚዘረፍባት
: በእርግጠኝነት በያንዳንዱ ባለ ስልጣን ስም የተመዘገበው ቢመለስ
በተለይ የአዲስ አበባው እና ኦሮምያ ዙርያ ግማሹን እንደሚያህል
ጥርጥር የለኝም
: እስኪ የትግራይ ተወላጅ ሆኖ አዲስ አበባ
ውስጥ እየኖረ ቪላ ባይኖረው
እንኩዋን ኮንዶሚኒየም የሌለው ?
: እዛው የተወለደው እና ያደገው ግን እጣ
ይወጣልኛል ብሎ ይጠብቃል!
5. የህክምና ፣ የማህበራዊ ዋስትና ፣የመኖር መብት ዋስትና፣ መጠለያ
የማግኘት ዋስትና፣ ……የሚባሉ ነገሮች ህልም እንጂ እውነታ
እንደሆኑ የማይታወቅባት
6. በኢትጵያ ካሉት ከ190 ያህል የአገሪቱዋን ኢኮኖሚ ከሚያንቀሳቅሱ
ምካምፓኒዎች እንደ
– ሲሚንቶ ማምረቻዎች (በሙሉ)
– መኪና መገጣጠሚያዎች(በሙሉ)
– የትራንስፖርት ድርጅቶች(ከ85%
በላይ)
– አስመጪና ላኪዎች(በሙሉ ማለት
ይቻላል)
– የልማት ማህበራት
– የባንክ አገልግሎት ሰጭዎች(1/3)
– የመጠጥ ፋብሪካዎች
– የህትመት ስራ
– የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪው
– በቢሊዮኖች የሚገመት ገንዘብን
የሚያንቀሳቅሰው የኮንስትራክሽን
መስኩ( በሙሉ ማለት ይቻላል)
ለምሳሌ፣
-: ሱር ኮንስትራክሽን
-: ተ/ ብርሃንና አምባዬ
-: ሰንሻይን
-: ሚድሮክ
-: ሳትኮን
-: ኣፍሮ ፂዮን
-: አፍሪካዊት
-: ራማ ኮንስትራክሽን
-: ዝቁዋላ
-: ዮቴክ ኮንስትራክሽን
……የመሳሰሉት
በሙሉ የአንድ ዘር ወይም
የገዚው ፓርቲ አባላት ባለሃብቶች
አርደሉምን
ጠቅለል ባለ መልኩ
– 66ቱ የኢህአዴግ የልማት ድርጅቶች
ሲሆኑ
– 75 ደግሞ በአስገራሚ ሁኔታ
በሼህ አላሙዲን ስም
ተመዝግበው የሚገኙ ናቸው
ታዲያ ይሄ ነገር ፍትሃዊ ነውን?
ይህ ኮሜንት ከመንግስት ጠጋ ያለና
-ኪንዶሚኒየም የወሰደ
-ያለ በቂ ማስረጃ ስራ ያገኘ
– የቀበሌ ቤት የተሰጠው
– ያለ በቂ ትምህርት የኮንስትራክሽ ፍቃድ ተሰጥቶት ኮንዶሚኒየም
ግንባታ እና እቃ አቅርቦት ላይ እየተሳተፈ ያለን
– በስሙ እና በቁዋንቁዋው ብቻ ከባንክ ብድር የተመቻቸለት
– መሬት በነፃ የተቀበለን
– አነስተኛ ግብር የሚከፍልን
– ቀረጥ ነፃ ለሌላው እየተከለከለ ለርሱ የሚፈቀድለትን
– በጨረታ ስም ስራ ተላልፎ ለርሱ የሚሰጠውን
– የውጭ ምንዛሪ በመድልዎ የሚያገኘውን
አይመለከትም
7. መብትህን ጠይቅ ይባላል ለመጠየቅ ግን ምንም አይነት መንገድ
ያልተዘጋጀለት፣ እንዲህ ሲመረው እና ሲያምፅ ግን ጠላት ተደርጎ
ሞርታር እና ታንክ የሚታዘዝባት
– ሰላማዊ ሰልፍ ለድጋፍ እንጂ ተበደልኩ ለሚል የማይፈቀድባት ሃገርከአንድ ጦማሪ የተገኘ
አይደለችምን
በመጨረሻም ንብረት ጠፋ ብላቹ ለምትንጨረጨሩ አንድ ጥያቄ
ልጠይቅ
የሰው ህይወት ዋጋው ስንት ነው? ንብረት ቢጠፋ ንብረት ይተካል ውድ
የሆነው የሰው ዋጋስ?
ፍትህ እና ነፃነት እግዚአብሔር ለሰዎች ከሰጠው ትላልቅ ስጦታዎች
መካከል ዋነኛዎቹ ናቸው ። እነዚህን አትውሰዱብኝ እያልኩ
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይይ እላለሁ
አበበ ጆቤ ትክክል ነው ይህን ጹሑፍ የጻፉት ሳሞራ ናቸው በሰው ያጻፉት::
This guy is one of the core TPLFites who does not believe in critics, change, and any new idea. He is a stubborn politician who takes EPRDf to the edge of the cliff. He does not have any substance or logical reasoning to argue with the concerned General idea of solution. One thing which puzzling me a politician who cannot agree to some points with his old fellow comrade then how come he will be open to new ideas from other group who think differently from his stagnant idea . It is time for openness, dialogue, and democratic action. Otherwise, you see the output of the current turmoil is the work of the writer of this article and the likes. In Democracy people is judging you and to visualize the blurring of current political, take back your mind to the time when you were fighting the Derge if you were a fighter or pass through liberation front.