የክብር ዶክትሬት ሸፍጥ እና መንደሬነት

በርግጥ የሰው ልጅ ለሚያበረክተው የላቀ አስተዋፅኦ እዉቅናና ክብር መሰጠቱ ይበል እሚያስብል ነገር ነው። በተለይ እንደኛ ዓይነት ባለ ሃገሩንና ህዝቡን ለዘመናት ሲያገለግል የኖረን ዜጋ በቀላሉ አሽቀንጥሮ በሚጥል ማሕበረሰብ እዉቅና መስጠት መጀመሩ መበረታታት አለበት። ሆኖም በየዓመቱ የክብር እየተባለ እየተሰጠ ያለው የክብር ዶክትሬት ግን በብዙዎች ዘንድ እየተወገዘ ቢሆንም ኣሁንም ዩኒቪርሲቲዎቻችን በተለመደው መንገድ እየነጎዱ ነው።

ይሄ የክብር ዶክትሬት የሚባል ጉዳይ መቀለጃና ወዳጅ ማፍርያ እየሆነ ነው። የክብር ዶክትሬት የሚሰጠው እጀግ የላቀ ሰብኣዊ ኣስተዋፅኦ ላደረገ ሰው ነው። አሁን እያያን ያለነው ግን እያንዳንዱ ዩኒቪርሲቲ የክልሉን ወይም ያካባቢዉን ተወላጅ የሚሸልምበት ኣሳፋሪ ድርጊት እየሆነ ነው። እያንዳንዱ ዩኒቪርሲቲ በየዓመቱ የኣንድ ወረዳ ህዝብ የሚሆን የሰው ብዛት የክብር ዶክትሬት ይሰጣል። Universal ፀጋዎች እና ክብሮች እንዲያስተምሩ የተቛቛሙት ዩኒቪርሲቲዎቻችን የመንደሬነት ማእክል፣ አመራሩም የመንደሬነት ባለሞያ፣ ድርጊቱም የወንዜነት ዶክትሬት መስጠት ሆኖ አረፈ። Universal ይቅርና የፌዴራል ተቛም መምሰል ኣቅትዋቸው የተራ መንደሬ ስራ መስራት ከጀመሩ ቆይተዋል። መንደሬነት ስብኣዊ ክብሮችን ስለማያቃቸው Universal መርሆዎችን አያከብራቸዉም።

ችግሩ የሚጀምረው ከኣመራር መረጣ ነው። ለምሳሌ መቐለ ወይም ባህርዳር ላይ የሚገኝ ዩኒቪርሲቲ የፈለገ ብቃት ያለው ሰው ቢሆን ያካባቢው ተወላጅ መሆን አለበት፤ ዩኒቪርሲቲ መሆኑ ይረሳና የክልሉ ፓርቲ መዋቅር ተቀጥያ በመሆን ያገለግላል፤ አስተማሪዎችም የተሻለ ታማኝ ለመሆን እንጂ የተሻለ ተመራማሪ ለመሆን የማይፈልጉበት ሁኔታ ይፈጠራል። ስንት ምርጥ ጭንቅላት በመንደሬ ኣመራርና በፓርቲ ጣልቃ ገብነት ይመክናል ወይም ይታፈናል። ይህ በሁሉም ዩኒቪርሲቲዎቻችን በተለያየ መጠን በስፋት ያለ ችግር ነው።እኔ እስከማዉቀው ድረስ ካዲስ አበባ ዩኒቪርሲቲ ዉጪ ሌሎች ዩኒቪሲቲዎች የሚመሩት ባካባቢው ሰው ነው፤ ባጭሩ ዩኒቪርሲቲዎቹ ዩኒቨርሳል ክብሮች ሳይሆኑ ባመራርም ባሰራርም መንደሬ ናቸው። አንደኛ በሽታቸው የፓርቲ ጣልቃ ገብነት ነው፤ ለምሳሌ አስተማሪዎች ይህንን የጉልበት ጣልቃ ገብነት ባይፈልጉትም ምንም ማድረግ እንዳይችሉ ተደርገዋል። ቢናገሩ ምን እንደሚመጣ ከራሴው ዩኒቨርሲቲ በላይ ማሳያ የለም።

ዩኒቨርሲቲዎች ለስብኣዊ ክብር የላቀ ዋጋ የከፈሉና ዓይነተኛ ለዉጥ ያመጡ ሰዎችን እንጂ በግልባጩ የሰው ልጅን ነፃነት በሚነፍጉ ሂደቶች የተሳተፉ ግለ-ሰዎችን መሸለም ከጀመሩ የመጨረሻቸው መጀምርያ ነው። ይባስ ብሎ ምንም አንፃራዊ ነፃነት የሌላቸው ዩኒቪሲቲዎች ተሸላሚዎቹ ኣካላት ናቸው በእጅ አዙር ራሳቸዉን እየሸለሙ ያሉት። በመላው ዓለም ለምትመረቁ ተማሪዎች እንዃን ደስ ኣላቹህ እላለሁ። ዩኒቪርሲቲዎቻችንን ደግሞ ዩኒቪርሲቲ ምሰሉ፤ የምትሰሩትን እወቁ፣ በየዓመቱ አታሳፍሩን ማለት እወዳለሁ።

******

more recommended stories