የወልቃይት የማንነት ጥያቄ – በታሪክና በህገ መንግስቱ

(ዘርአይ ወልደሰንበት)

1. የማንነት ጥያቄ ባሕርይና ስለሚያስገኚው መብት

1.1. የማንነት ጥያቄ ባሕርይ ና ጥያቄውን የማቅረብ መብት

1.2 ስለ ብሄር ማንነት ዕውቅና ውጤት

1.3 ስለብሄር ማህበረሰብ አባልነት

2. የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ

2.1 የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ ባህርይና ጥያቄውን የማቅረብ መብት

2.2 የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ (የድንበር ዉዝግብ) የሚፈታበት መንገድ

2.3 የድንበር ውዝግብ መወስኛ መስፈርት

3.ታሪክ ቀመስ ዳሰሳ ባጭሩ

4. መደምደምያ

1. መግቢያ

የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? የድንበር አከላለል ለውጥ(የድንበር ውዝግብ)ጥያቄስ ምንድን ነው? የኢትዩጵያ ህግስ እንዴት ነው የሚጠብቃቸው? የዚህ ማስታወሻ ዓላማ እነዚህን ጉዳዩች ስለሚመለከቱት የህግ ክፍሎች በማጥናትና ስለአተረ¹ጎማቸው አስተያየት በማቅረብ እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ ነው፡፡ ከእነዚህ ባሻገር ይህ ማስታወሻ ስለ ትግራይ ህዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪካዊ ዳሰሳ ባጭሩ አድር¹ል፡፡

ይህን ማስታወሻ ለመጰፍ ያነሳሱ ነገሮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ተወካዮች ነን ባሉ ስዎች በቀረበለት ገዘ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 20 ድንጋጌ መሰረት የማንነት ጥያቄው በክልሉ በደረጃው ባሉ የአሰተዳደር እርከኖች ታይቶ ውሳኔ ማግነት የሚገባው በመሆኑ ጉዳዩ በትግራይ ክልል እንደታይ ብሎ በመወስን ማስተላለፉ እና ማንነቴ ናቸው፤፤ በዚህ የተነሳ ዋናው ጥያቄ  የሆነውን የማንነት ጥያቄ ምንነትና የድንበር አከላለል ለውጥ(የድንበር ውዝግብ)ጥያቄ ምንነት በመመርመር ስለአተረጎገማቸው አስተያየት ማቅረብ የወደድኩ ሲሆን ወደዚህ ዝርዝር ጉዳይ ምልከታ ከመግባታችን በፊት ስለ ኢትዩጵያ ቀድሞ አገዛዞች መሰረታዊ ባህርይ እና ስለአሁኑ የኢትዮጲያ የፖለቲካ ስርአትና በኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሀገር ግንባታ የተቀመጡት ድንጋጌዎች መሰረታዊ ጽንሰ መጠነኛ ምልከታ ብናደርግ የማንነት ጥያቄ ባህርይና የብሔሮች መብቶች ፅንሰ ሃሳቦችን በሚገባ ለመረዳት የሚያስችለን ሁኔታ ይፈጥርልናል የሚል ተስፋ አለኝ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ከሰኔ 24 እስከ 28 ቀን 1983 ዓ.ም በተደረገው ጉባኤ አማካይነት ኢትዩጵያ በአዲስ መልክ የሽግግር ጊዜ እንዲኖራት ታስቦ የሽግግር ጊዜ ቻርተር ታወጀ፡፡ በዚህ ቻርተር መሰረት የኢትዩጵያ ብሔረሰቦች ሁሉ የራስን ዕድል በራሳቸው የመወሰን መብት እንዲኖራቸውና ሲፈልጉም እንዲገነጠሉ እና ነፃ መንግስት እንዲያቋቁሙ ተፈቅዷል፡፡ ይህም ለኢትዩጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍን ከፍቷል፡፡

ቀጥሎም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የታወጀ ሲሆን ከዚህ ህገ መንግስት ውስጥ ከተደነገጉት መሰረታዊ መርሆዎች ሁሉ ዋነኛው ምሶሶ መርሆ የብሔሮች የራስ ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል ነው፡፡የዚህን ህገ መንግስታዊ መርሆ መሰረታዊ ይዘትና ከዚህ አኳያ የፌዴራሉ ህገመንግስት የደነገጋቸውን ድንጋጌዎችና ሌሎች የበታች ህጎችን በተሟላ መልኩ መገንዘብ ያሻል፡፡ ኢትዩጵያ የበርካታ ብሔሮች ሃገር ሆና ለብዙ ዘመናት ቆይታለች፡፡ በብሔሮች መካከል የሚፈጥረው አስተዳደራዊ ግንኙነት በየጊዜው በነበሩ አገዛዞች መልኩን እየቀያየረ የተፈጠረ ቢሆንም ሁሉም የቀድሞ የአገዛዝ ዘይቤዎች በመሰረታዊ ይዘታቸው ኢ-ዲሞክራሲያዊ፣ ጨቋኝና አድሎአዊ ነበሩ፡፡ ብሔሮች አንድነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንዲገልፁ ከማድረግ ይልቅ በግዳጅ አንድነታቸውን እንዲገልፁና እንዲጋቱ ለማድረግ የቻለውን ሁሉ ከመደረጉም በላይ ብሔሮች በዚህ ሁኔታ በአንድነት ስር በነበሩበት ጊዜ የየራሳቸውን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ እና መልክዓ ምድር በአጠቃላይ ብሔራዊ እሴቶቻቸውን ሆን ተብሎ በአስተዳደራዊ መንገድ ወይም ግንኙነት እንዲያጡ ተሞክሯል፡ በአንዳንዶቹ ላይ ተሳክቷል፡፡ በሌላ አገላለፅ ከብሔር ማህበረሰቦች አንዳንዶቹ ወድመዋል፡፡ የአናርያ ግዛት ንጉስ ፈጠጋር፣ ደዋሮ እና ባሌ ከገፀምድር ጠፍተዋል፡፡ ታሪክ ያከበራቸው የቦሻ፣ የደቦ፣ የቋራ፣ የሄራ፣ የፈላሻ እና የጋፋት ህዝቦች ጨርሶ አልቀዋል ወይም ከሌሎች በደም ተቀላቅለዋል ወይም ደግሞ እንደ አርጎባዎች፣ ባይሶዎች፣ በላዎችና ጋዲቶዎች ተቀነጣጥበው አንሰው የተረፉት በመቶ የሚቆጠሩ ናቸው፡፡ በእነዚህ አገዛዞች የተነሳ በዚያን ጊዜ በሰፊው የታወቁ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የቦታ ስሞች ለምሳሌ እንደ ኩልጎራ፣ ዋዝ፣ ሶጋየአሉ ደብዛቸው ጠፍቷል፡፡

የዚህ ጉራማይሌ ማህበረሰብ አባላት መትረፍ መቻላቸው እጅግ የሚያስደንቅ ነው፡፡ በተራሮችና በጅረቶች ከለላ ተጠብቀው በዘመኑ ከነበራቸው ችግርና በአከባቢያቸው ጉዳይ ተወጥረው የቀድሞ አባቶቻቸው በአዋሰኗቸው ክፍለሃገራት እየኖሩ አብዛኞቹ ከነበሩበት ሳይነቃነቁ ቆይተዋል፡፡

ሃገር ግንባታ (ምስረታ) ብሔሮች አንድነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው ባላቸውና በሚኖራቸው የጋራ ዓላማና ጥቅም፣ ባላቸው የወንድማማችነት መንፈስ ላይ ተመስርቶ እንዲገነባ ከማድረግ ይልቅ የብሔሮች ነባራዊ ህልውና እንደሌለ በመቁጠር፣ ባለማክበር፣ እንዳይኖሩ በማድረግ ጨቋኝ በሆኑ አስተዳደራዊ መሳሪያዎች በመጠቀም አገር ለመገንባት ተሞክሮ የብዙዎች ደም ፈሷል፡፡

በዚህ አገር አጥፊ አካሄድ የተከፉ ብዙ ብሔሮች በቋንቋችን እንጠቀም፣ ባህላችንን እናንፀባርቅ፣ ታሪካችንን እንግለፅ፣ እናዳብር እንዲሁም በተወሰኑ ጉዳዩች ራሳችንን በራሳችን እናስተዳድር እና ተገደን ኢትዮጵያዊነትን ልንቀበል (ልንጋት) አይገባም በማለት ለዘመናት በተናጠልና በተደራጀ መንገድ እልህ አስጨራሽ ትግል አድርገው በስተመጨረሻ ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም ድል አድርገው በኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ከፍተዋል፡፡

የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል፣ የብሔሮች ጥያቄ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ብቅ ያለው ቻርተሩ ሆነ ህገመንግስቱ ሲፀድቅ አይደለም፡፡ ጥያቄው በንጉስ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ጊዜም ሆነ በደርግ አገዛዝ ጊዜም የነበረ ጥያቄ ነው፡፡

በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ ምናልባትም ከዓለም ተለይታ የራሷ የሆነ ከጥንታዊ ባህሏና ልማዷ ፅንሰ ሃሳብ ጋር የተዛመደ ህገመንግስት አውጃ በስራ ላይ በማዋል ላይ ትገኛለች፡፡ ይህም ኢትዮጵያ በቀረው የአፍሪካ አህጉር ከሚገኙት ክፉውን ከበጎ ሳይለዩ የውጭ ዓለም ያመጣውን የፖለቲካ አቋሞች በሁለንተናው አሜን ብሎ የመቀበል ልማድን አሽቀንጥራ በመጣል የራሷ የሆነ አዲስ የፖለቲካ አቋም ለመፍጠር ችላለች፡፡ በዚህም ከኢትዮጵያ ብሔሮች ጋር የማይስማሙ የውጭ ዓለም ያመጣውን የፖለቲካ አቋሞች እንዲሁ ለስሙ ብቻ ሳይታሰብና ሳይጠና የኢትዮጵያ ብሔሮች ጥንታዊ የአገዛዝ ፅንሰ ሐሳብ በጠቅላላ እና ድንገተኛ የማድረግና የመቀበል ሲወርድ ሲዋረድ የነበረውን አስተሳሰብ ከመሰረቱ መቀየር ተችሏል፡፡ይህ አይነት ድንቅ ስራ በአፍሪካ ከዚህ በፊት ያልተደረገ ሲሆን በኢትዮጵያ ባለፉት 25 ዓመት ለመፈፀም ተችሏል፡፡

ልዩነትን በሰፊው የሚያቅፍና ሁሉን ጠቅሎ በማዕከል የማይዘው ይህ አዲስ ህገመንግስት በሚገባ በመከተልና በስራ ላይ በህገመንግስቱ በተሰጠው ቅርፅ ልክ በማስፈፀም ኢትዮጵያ ከአሮጌ ወደ አዲስ ጎዳና መሸጋገር የሚፈጥረውን ችግርና አለመረጋጋት ለማቃለል ሰሙም ሰልቶች ያስፋልጋሉ፤ እንደምትችልም ተስፋ አደርጋለሁኝ፡፡ እዚህ ላይ አንድ ታዋቂ የሕግ ሊቅ ያለውን መጥቀስ እሻለሁኝ፡፡ ይህ ሊቅ አዲስ ህጋዊ ልብስ ምንም ተወዳዳሪ በሌላቸው የህግ ልብስ ሰፊዎች ቢሰፋም የማህበራዊ ኑሮን አካል መኮስኮሱ የማይቀር ነው ብሏል፡፡ እነዚህ በአዲሱ ስርዓት የተነሳ የሚኮሰኩሳቸው ሰዎች አዲሱ ስርዓት የኢትዮጵያ ስልጣኔ ወደ ፊት መራመድና ዘመናዊ መሆን እንዲሁም መረጋጋት ላይ በዋናነት ችግር ያመጣል  ብለው ሳይሆን አሮጌው ስርዓት ያስገኝላቸው የነበረ ቁሳዊና ሞራላዊ ጥቅም ዳግም አፈር ልሶ እንዳይነሳ በኮንክሪት መቃብር ስር ድንጋይ ተንተርሶ በመቀበሩ ነው፡፡ ለጊዜው እዚሁ ላይ አቁመን ወደ ዋናው ጉዳያችን ምልከታ እንግባ፡፡

1. የማንነት ጥያቄ ባሕርይና ስለሚያስገኚው መብት

1.1. የማንነት ጥያቄ ባሕርይ ና ጥያቄውን የማቅረብ መብት

የማንነት ጥያቄ ምንድን ነው? ጥያቄውንስ የማቅረብ መብት ያለው ማን ነው? የማንነት ጥያቄን ለመወሰን የሚያስፈልጉ መስፈርቶች ምንድናቸው? ማንነት ዕውቅና ማግኘቱ ምንን ያገኛል? ጥያቄውን የመወሰን ስልጣን የማን ነው? የሚወሰነውስ ምን ስነስርዓት በመከተል ነው ሚሉትን ጥያቄዎች በዝርዝር ከዚህ በታች መመልከት እንሞክራለን፡፡      

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስትም ሆነ ሌላ የኢትዩጵያ ህግ ማንነት (identity) የሚለው ቃል ትርጉምን በጣም ግልፅ በሆነ ሁኔታ አይገልፁም፡፡ አንድ ሰው ብዙ ማንነቶች ሊኖሩት ይችላሉ፤ ይኖሩታልም፡፡ አንድ ማንነት በጉልህ የሚታየው ከሌላው ጋር ሲነፃፀር እንደመሆኑ መጠን፤ አንድ ሰው ወይም ቡድን ማንነቱን የሚገልፅበት መንገድ እንደሁኔታው ይለያያል፡፡ ጥያቄው ዜግነትን ሲከተል፤ ዜግነታዊ ማንነትን ያስቀድማል ማለት ነው፡፡ ብሔራዊ ማንነት የሚመለከት ከሆነ ብሔራዊ ማንነቱን ያንፀባርቃል፡፡ ብሔራዊ ማንነት (ethnic identity) በሁለት ይከፈላል፡፡ ይኸውም የብሔር ማህበረሰብ ማንነት(ethnic community identity)ና የብሔር ማህበረሰብ አባልነት (ethnic community membership )ተብሎ ይከፈላል፡፡  

በኢትዮጲያ በጠቅላላ አጠቃቀሙ መሰረት ማንነት(identity)  አንድ ማህበረሰብ ራሱን ከሌሎች ለመለየትና ለማወቅ እንዲቻል ለማድረግ የሚጠቀምበት ብሔራዊ ማንነት (ethinic identity) ማለት ነው፡፡ በስልጤ የማንነት ጥያቄ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሰጠው ውሳኔ የማንነት ጥያቄ የሚባለው የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ መሆኑን ገልጸል፡፡የማህበረሰብ ብሔራዊ ማንነት ቋንቋን ጨምሮ ባህልን፣ ማንነትን፣ ስነልቦናን እና በአብዛኛው የተያያዘ መልክዓ ምድርን መሰረት ተደርጎ የሚገኝ አቋም ነው፡፡ የብሔር ማህበረሰብ ማንነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ መሰረታዊ ቦታ አለው፡፡ ለዚህም ነው የኢትዮጵያዊነት ማንነት በብሔራዊ ማንነት ላይ የተመሰረተ ነው የሚባለው፡፡ የኢትዮጵያዊ ማንነት የሚኖረው በቅድሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ማንነት ሲኖር ነው፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያዊ ማንነትና በብሔራዊ ማንነት መካከል መቆራኘት (መቆላለፍ) አለ፡፡

ለዚህ ፅሑፍ (አንቀፅ) ያህል ብሔራዊ ማንነት የሚለው ቃል በአንድ ማህበረሰብና በግለሰቦች መካካል በብሔራዊ ማንነት መለኪያዎች አማካኝነት የዝምድና ግንኙነትን ያመለክታል፡፡ ብሄራዊ ማንነት ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከምኞት (ከፍላጎት ወይም ከምርጫ) የሚገኝ አቋም ሲሆን አቋሙን የሚያገኘው በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ብሔራዊ ማንነት ጥያቄ ማለት በፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 39/5/ መስራት የሚቀርብ የብሔር ማህበረሰብ አቋም (status) ጥያቄ ማለት ነው፡፡ አሁን የምንመለከተው በዋናነት ስለብሔራዊ ማንነት ነው፡፡ በቅድሚያ ስለብሔራዊ ቡድን (ማህበረሰብ) ማንነት እንመልከትና ለጥቆ ስለግለሰባዊ ብሔራዊ ማንነት ባጭሩ ምልከታ እናደርጋለን፡፡

በአሁኑ ጊዜ አንድ የማህበረሰብ ልዩ ማንነት አንድ ወይም ሁለት ተግባሮችን ይፈፀም ይሆናል፡፡ አንደኛ የአንድ ማህበረሰብን ምንነት ለይቶ ያስታውቃል፡፡ ሁለተኛ ደግሞ የአንድን ማህበረሰብ ጠቅላላ ምንጭን ለይቶ ያስታውቃል፡፡ በዚህ አባባል መሰረት የብሔር ልዩነት የአንድን ማህበረሰብ የተለየ ምንጭ እንኳን ባይሆን ጠቅላላ ምንጭ ያመለክታል ሊባል ይችላል፡፡ ሆኖም ከዘመኑ የብሔር ፖለቲካ ማህበረሰብ ውስጥ ዋናው ተግባሩ አንድ የብሔር ማህበረሰብ ራሱን በማንነቱ በመመስረት ለመለየት ወይም ለማስታወቅ እንዲረዳው ማህበረሰቡ ከሌሎች ማህበረሰቦች ለመለየት እንደሚያስችለው ነው፡፡

ለብሔራዊ ማንነት ጥያቄ (አቤቱታ) አግባብነት ያላቸው ህጎች ሁለት ናቸው፡፡ አንደኛው  በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ የተደነገገው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 19/1/፣ 20፣ 21 እና 22 ናቸው፡፡ እነዚህም የማንነት ጥያቄ ህጋዊ መሰረትና ምንጭ ናቸው፡፡ የፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 39/1/ ላይ እንደተጠቀሰው ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል መብት ያለገደብ አለው፡፡ ይህ መብት ሁለት ነገሮችን የሚያጠቃልል ነው፡፡ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ ብሔሮች በኢትዮጵያ ስር ሆነው በውስጥ ጉዳያቸው ራሳቸውን በራሳቸው በሰፈሩበት መልክዓ ምድር የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን ያላቸው መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ማንኛውም ብሔር ያለ ገደብ በፈለገበት ጊዜ በህገመንግስቱ በተቀመጠው ስርዓት መሰረት ለመገንጠል (መነጠል) የሚችል መሆኑን ይገልፃል፡፡

እዚህ ላይ ጥያቄው የዚህ መብቶች ባለቤት ማንነው? የሚል ነው፡፡ የነዚህ መብቶች ባለቤት ማን እንደሆነ በሕገመንግስቱ ከአንቀፅ 39/1/ እስከ /4/ ድረስ ተደንግጓል፡፡ በነዚህ ድንጋጌዎች መሰረት እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ የብሔር መብቶች ባለቤት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ለመሆኑ ብሔር፣ብሔረሰብ ወይም ህዝብ ማን ነው? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ላይ ተቀምጧል፡፡የዚህ ህገመንግስት አንቀፅ 39/5/ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ ለመባል ሊሟሉ የሚያስፈልጉ አምስት መስፈርቶች አስቀምጧል፡፡ እነዚህም ቋንቋ፣ ባህል፣ የህልዉና አንድነት፣ የስነልቦና አንድነትና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር መስፈሩ ናቸው፡፡እነዚህን መስፈርቶች በሙሉ የሚያሟላ ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብ ማንነት(አቋም) ያገኛል፡፡ ከነዚህ መስፈርቶች አንዱን ያላሟላ ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብ አቋምን ጨርሶ ሊያገኝ አይችልም፡፡ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ዕውቅና የማግኘቱ አስፈላጊነት የብሔር መብቶችን ለመጠቀም ነው፡፡ የብሔር ማህበረሰብ አቋም እውቅና ያላገኘ ማህበረሰብ የብሔሮች መብቶች ሊኖሩት አይችልም፡፡በዚህ ክፍል ውስጥ የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ የሚወሰንበት መሰረታዊ መስፈርት/መስፈርቶች ምን እንደሆነ/ኑ ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገመንግስት ህብረብሔራዊ ፌዴራሊዝም የመገንባት አቋም ወስዷል፡፡ ከዚህ ዓላማ ተነስቶ ስለብሄር ማህበረሰብ ማንነት (ባህርይ) በአንቀፅ 39/5/ ላይ ትር¹ሜ ሰጥቶታል፡፡ የብሔራዊ ማንነት የዕውቅና ጥያቄ መሰረትም ይሄው የህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ነው፡፡ በዚህ ሕገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ መሰረት የብሔር ማህበረሰብ ተብሎ ዕውቅና ለማግኘት መሟላት ያለባቸውን አምስት መስፈርቶች አደራጅቷል፡፡ እነዚህም፡-

– ቋንቋ

– ባህል

– የሕልውና አንድነት

– የስነልቦና አንድነት

– በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር መኖር ናቸው፡፡

የማንነት ዕውቅና ሊሰጥ የሚችለው ጥያቄ አቅራቢው ማህበረሰብ ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ተጨባጭ ሁኔታዎችና ተጨባጭ ያልሆኑ ሁኔታዎች አሟልቶ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት ጥያቄው የሚወሰነው በገለልተኛ አካል አስተያየት እና በራሱ በጥያቄው አቅራቢ ህዝብ አስተያየት ነው ማለት ነው፡፡ ሆኖም የፌዴሬሽን ምክር ቤት በስልጤ ህዝብ የማንነት ጥያቄ  ላይ በሰጠው ውሳኔ የማንነቴ ይታወቅ ጥያቄ አከራካሪ በሆነ ጊዜ ጥያቄውን ያቀረበው ማህበረሰብ አባላት በሚያደርጉት ቀጥተኛ ተሳትፎ በሕዝብ ውሳኔ መወሰን ይገባዋል ሲል ወስኗል፡፡ በዚህም ውሳኔ መሰረት አከራካሪ የሆነ የማንነት ጥያቄ ያለገለልተኛ አካል አስተያየት ጥያቄው በራሱ በጠያቂው ማህበረሰብ ግላዊ አስተያየት ሊወሰን ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በአንቀፅ 39/5/ ላይ የተደነገጉትን ተጨባጭ የሆኑትን የቋንቋ፣ የባህል እና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የመኖርን መስፈርቶች ቸል መባላቸውን በግልፅ ያሳያል፡፡ ህገመንግስቱ እንደዚህ ዓይነት የማንነት ጥያቄዎች የማንነት ጥያቄ ባቀረበው ማህበረሰብ ህዝበ ውሳኔ ብቻ እንዲወሰኑ አንዳችም ድንጋጌ ላይ በግልፅ ሆነ በዝምታ የገለፀው ነገር የለም፡፡ ህገ መንግስቱ የመገንጠል ጉዳይና ክልል የማቋቋም ጉዳይ በህዝበ ውሳኔ በስተመጨረሻ እንዲወሰኑ ደንግ¹ል፡፡ ህገመንግስቱ በእነዚህ ጉዳዩች ላይ ህዝበ ውሳኔ ተደርጎ ይወሰን ማለቱ በምንም አመክንዩ የብሔራዊ የማንነት ጥያቄ በህዝበ ውሳኔ ብቻ ይወሰኑ ብሏል ሊባል አይችልም፡፡

ህገመንግስቱ በአንቀፅ 39/5/ ላይ የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ (የብሔር ማህበረሰብ አቋም ጥያቄ) የሚወሰንባቸውን አምስት መሰረታዊ መስፈርቶች አስቀምጧል፡፡ ከእነዚህ አምስት መሰረታዊ መስፈርቶች ባህርይ መረዳት እንደሚቻለው የብሔር ማህበረሰብ አቋም ጥያቄ ሊወሰን የሚገባው ጠያቂው ማህበረሰብ አባላት በሚሳተፉበት ህዝበ ውሳኔ ብቻ ሳይሆን በገለልተኛ አካል ውሳኔም ጭምር ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ህገ መንግስቱ የደነገገዉ የብሄራዊ ማንነት ጥያቄዎች በሶስተኛ ወገን ዳኝነትና በህዝብ ዉሳኔ እንደወሰኑ ነዉ፡፡ ገለልተኛ አካሉ የሚወስነው ጠያቂው ማህበረሰብ የቋንቋ፣ የባህልና የአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር መኖር መስፈርቶች መሟላት ወይም አለመሟላታቸውን ሲሆን ጠያቂው ማህበረሰብ ደግሞ በህዝበ ውሳኔ የሚወሰነው የማህበረሰቡ ህልውና አንድነትና የስነልቦና አንድነት ምን እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም የቋንቋ፣ የባህልና የአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር መኖር መስፈርቶች በህዝበ ውሳኔ ሊወሰኑ የሚችሉ ነገሮች ጨርሶ ባለመሆናቸው ነው፡፡ በአጠቃላይ የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ የሚወሰነው ከዚህ በላይ በተመለከተው አግባብ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ማግኛ/መወሰኛ መስፈርቶች በገለልተኛ አካል ውሳኔ እና በጠያቂው ማህበረሰብ ውሳኔ መሰረት በሙሉ አንድ ላይ ተሟልተው መገኘት ወይም አለመገኘት ላይ በመመስረት ነው፡፡ እነዚህ መስፈርቶች በሙሉ ተሟልተው ከተገኙ ጥያቄው ተቀባይነት አግኝቶ የብሔራዊ ማንነት ዕውቅና ይሰጣል አለበለዚያው ጥያቄው ተቀባይነት አጥቶ የብሔራዊ ማንነት ዕውቅና ይነፈጋል፡፡

የመስፈርቶቹ አወሳሰን ቅደም ተከተል አለው፡፡ የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ በቀረበ ጊዜ በቅድሚያ የክልል ምክር ቤት ወይም በፌዴሬሽን ምክር ቤት ሦስት ተጨባጭ የሆኑ መስፈርቶች በሙሉ የተሟሉ ስለመሆኑ ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማድረግ መወሰን አለበት፡፡ በዚህ አግባብ እነዚህ ሦስት መስፈርቶች በሙሉ ተሟልተው ያልተገኙ መሆኑ ከተወሰነ ወደ ቀጣዩ ህዝበ ውሳኔ መሄዱ አግባብነት የለውም፡፡ ወደ ህዝብ ውሳኔ የሚኬደው ከዚህ በላይ በተጠቀሰው አግባብ በወሳኙ አካል ሦስቱ ተጨባጭ መስፈርቶች ተሟልተዋል ተብሎ ከተወሰነ ብቻ ነው፡፡ በዚህ መልኩ ህዝበ ውሳኔ ተደርጎ ማህበረሰቡ ውሳኔን ከገለፀ በኃላ በጥያቄው ላይ ውሳኔ ይሰጣል፡:

የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ ዕውቅና የማግኘት ጥያቄ ብቻ ነው፡፡ ይህ እውቅና ማግኘት ደግሞ የብሔር መብቶችን ያጎናፅፋል፡፡ የብሔር መብቶች ደግሞ በመሰረታዊነት በፌዴራሉ ህገመንግስት  በአንቀፅ 39 ከንዑስ አንቀፅ (1) እስከ (4) ድረስ ተዘርዝረዋል፡፡ እነዚህን የብሔር መብቶች ለማግኘት የግድ በቅድሚያ ማህበረሰቡ የብሔር ማህበረሰብ አቋም  ዕውቅና ማግኘት ይኖርበታል፡፡ በዚህም የተነሳ በብሔራዊ ማንነት ጥያቄበብሔር መብቶች ጥያቄ ረገድ ልዩነት መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡የብሔር  መብቶችን ማግኘት የሚቻለው የብሔር ማህበረሰብነት ዕውቅና ከተገኘ በኃላ በመሆኑ የብሔር ማህበረሰብ ዕውቅና ይሰጠኝ ጥያቄና የብሔር መብቶች ጥያቄ በአንድ ላይ ሊቀርቡ ጨርሶ አይገባም፡፡ ምክንያቱም ገና ያልተገኘ መብትን ልጠቀም ብሎ መጠየቅ የማይቻል በመሆኑ ነው፡፡

እዚህ ላይ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ዕውቅና ማግኛ/መወሰኛ መንገዶችን ምን ምን እንደሆኑ መጠነኛ ቅኝት ማድረጉ ተገቢ ይመስላል፡፡ እስከ አሁን ባለው ልምድ በተለያዩ መንገዶች እውቅና ሲሰጥ ቆይቷል፡፡በመጀመሪያ የፌዴራሉ ህገመንግስት ራሱ በቀጥታ በስም እውቅና የሰጣቸው የብሔር ማህበረሰቦች ያሉ ሲሆን እነሱም በህገመንግስቱ አንቀፅ 47/1/ ላይ እንደተጠቀሱት ትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሱማሌ፣ ቤንሻንጉል(በርታ)፣ ጉሙዝና ሐረሪ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውጭ ህገመንግስቱ በጥቅሉ እውቅና የሰጣቸው የብሔር ማህበረሰቦች እንዳሉ ከህገመንግስቱ፣ ከህገመንግስቱ ማብራሪያና ከህገመንግስቱ ቃለ ጉባኤዎች በመመልከት መገንዘብ ይቻላል፡፡ በ1987 ዓ.ም የህገመንግስቱ ማብራሪያ ላይ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ውስጥ 45 የብሔር ማህበረሰቦች እንዳሉ ጠቅሷል፡፡ በዚህም ነዉ፣ በህገመንግስቱ አንቀጽ 47(2) ላይ በህገመንግሰቱ አንቀጽ 47(1) ስር በተመለከቱት ዘጠኝ ክልሎች ዉስጥ የተካተቱት ብሔሮች በማናቸዉም ጊዜ የየራሳቸዉን ክልል የማቋቋም መብት አሏቸዉ ተብሎ የተገደነገገዉ፡፡ በዚህኛዉ መንገድ የብሔር ማህብረሰብ አቋም (status) ዕውቅና የሚሰጠዉ/የሚገኘዉ ማህበረሰቡ አቤቱታ/ጥያቄ ባላቀረበበት ሁኔታ ነዉ፡፡

ሁለተኛው የብሔር ማህብረሰብ አቋም (status) ዕውቅና ማግኛ/መወሰኛ መንገድ የእውቅና ጥያቄ አንድ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ያላገኘ ማህበረሰብ የእዉቅና ጥያቄዉን በቅድሚያ በሰፈረበት መልክዓ ምድር ውስጥ ለሚገኘው ክልላዊ ምክር ቤት በማቅረብ ነው፡፡የብሔራዊ ማንነት ጥያቄው በቀረበ ጊዜ ጥያቄዉ አከራካሪ እንዳልሆነ በክልሉ ም/ቤት በታመነ ጊዜ ያለህዝብ ውሳኔ በሚመለከተው ክልል ምክር ቤት ዕውቅና ሊሰጠው ይችላል፡፡ በዚህ አግባብ መሰረት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ም/ቤት በቅማንት የብሔር ማህበረሰብ አቋም ጥያቄን ያለህዝብ ዉሳኔ እዉቅና ሰጥቷል፡፡ ጥያቄዉ አከራካሪ መሆኑ በሚመለከተዉ የክልል ም/ቤት በታመነ ጊዜበሌላ በኩል የብሔራዊ ማንነት አቤቱታ በህዝብ ውሳኔ አማካኝነት ሊወሰን ይችላል፡፡ በዚህኛዉ መንገድ ደግሞ የስልጤ የማንነት ጥያቄ በህዝብ ዉሳኔ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡

የብሔር ማህብረሰብ አቋም (status) ዕውቅና አቤቱታው በህዝበ ውሳኔ ይወሰን ቢባል ማነው የህዝበ ውሳኔው ላይ ተሳትፎ የሚያደርገው የሚለው ጥያቄ የመጀመሪያ ጥያቄ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ የአመራረጣቸውስ ሁኔታ እንዴት ነው የሚለውም መሰረታዊ ጥያቄ ይመስላል፡፡ ለምሳሌ የወልቃይት የአማራ ብሔርተኝነት ጥያቄ ብሎ ነገር አለ ቢባልና ጥያቄው በህዝበ ውሳኔ ይወሰን ቢባል ምናልባትም በህዝበ ውሳኔው ላይ ሊሳተፉ የሚችሉት በወልቃይት የሚኖሩ አማራዎች ብቻ ናቸው ወይስ በመላ አገሪቱ የሚገኙ አማሮች ናቸዉ ወይስ በወልቃት ወረዳ ዉስጥ የሚገኙ ማናቸዉም ነዋሪ ኢትዮጲያዊን ናቸዉ?፡፡የእነዚህ አመራረጣቸውም ለክልሉ የተተወ እንደሆነ የፌዴሬሽን ም/ቤት በስልጤ የማንነት ጥያቄ ላይ አመልክቷል፡፡

ከዚህ ባሻገር፣ የፌዴሬሽን ም/ቤት አከራካሪ ባልሆነ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ላይ በራሱ ተነሳሽነት እውቅና ሲሰጥ ቆይቷል፡፡እንዲሁም በህገመንግስቱ አንቀፅ 62/3/ መሰረት አከራካሪ በሆኑ የብሔር ማህበረሰብ ዕውቅና ጥያቄ ላይ የመጨረሻ ዕውቅና የመስጠት ስልጣን አለው፡: 

በአጠቃላይ የማንነት ፅንሰ ሐሳብ ልዩ መሆኑ ነው፡፡ በለላ አገገላፅ የአንድ ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ለማግኘት ዋና ተፈላጊ ነገር ልዩ (distinctiveness) መሆኑ ነው፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገመንግስትና የክልሎች ህገመንግስት ይህን ተፈላጊ ነገር የያዙትንና ያልያዙትን ማህበረሰቦች የሚለዩ ደንቦችን አደራጅቷል፡፡ በዚህም መሰረት አንድ የብሔራዊ ማንነት ዕውቅና ይሰጠኝ ጥያቄ መቅረብ ያለበት ጠያቂው አካል ከሌሎች ዕውቅና ካገኙ የኢትዮጵያ ብሔር ማህበረሰቦች የተለየ የሆነ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ አንድ ማህበረሰብ ልዩ ባህርይ አለው ወይም የተለየ ነው ብሎ የሚወሰነው በአንቀፅ 39/5/ ስር በተቀመጡት አምስት መመዘኛዎች (መስፈርቶች) ነው፡፡ እነዚህም መስፈርቶች ቋንቋ፣ ባህል፣ ማንነት፣ የስነልቦና አንድነትና መልክዓ ምድር ናቸው፡፡ ህገመንግስቱ የማንነት ጥያቄን በተመለከተ ካስቀመጣቸው አምስት መስፈርቶች ሦስቱ ማለትም ቋንቋ፣ ባህልና መልክዓ ምድር ተጨባጭ (የሚዳሰሱ) ሁኔታዎች ሲሆን ማንነት ደግሞ ከፊል ተጨባጭ እና ከፊል ተጨባጭ ያልሆነ ሁኔታ ነው፡፡ አምስተኛው መስፈርት የስነልቦና አንድነት ሲሆን ይህ በግልፅ የማይጨበጥ ሁኔታ (subjective condition) ነው፡፡

በመሆኑም ህገመንግስቱ የማንነት ጥያቄን በተመለከተ ካስቀመጣቸው መመዘኛዎች ውስጥ ተጨባጭ የሆኑ ሁኔታዎች በሙሉ በገለልተኛ ሰው አስተያየት የሚመጠኑ ሲሆኑ ተጨባጭ ያልሆኑ ሁኔታዎች ደግሞ በገለልተኛ ሰው አስተያየት የሚመጠኑ ሳይሆን ጠያቂው ማህበረሰብ በራሱ የሚመጥነው ሁኔታ ነው፡፡ ማህበረሰቡ ልዩ መሆኑን ካረጋገጠ ወይም መሆኑ ከተረጋገጠ ልዩነት ማህበር ወይም የትብብር ምልክት ሆኖ ያገለግላል፡፡

በአጠቃላይ የማንነት ፅንሰ ሐሳብ ልዩ በመሆኑ በኢትዩጵያ ውስጥ በአንድ የብሔር መብቶች ለመጠቀምና ልዩነታቸውን ለመጠበቅ የሚፈልጉ የብሔር ማህበረሰብነት ዕውቅና ያላገኙ ማህበረሰቦች በቅድሚያ የማንነት ዕውቅና ይሰጠን ጥያቄ (አቤቱታ) በየደረጃው በሚመለከታቸው የክልልና የፌዴራል አስተዳደሮች ዘንድ በማቅረብ እውቅና በማሰጠት ማስታወቃቸው የግድ ነው፡፡ ዕውቅና ላልተሰጣቸው ማህበረሰቦች የብሔር መብቶችን ከመስጠታችን በፊት ማህበረሰቦች ልዩ (ብሄር) መሆናቸውን ስልጣን ባለው አካል ማረጋገጥ አለባቸው፡፡ በብሔር መብቶች ለመጠቀም መኖር የሚባል ልዩ መሆን ሁኔታ የብሔር መብቶች በሚገባ እንዲጠበቁ ሲፈለግ እውቅና ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም በዕውቅና ሰጪ አካላት አማካኝነት ለዕውቅና የቀረበው ማንነት በስራ ላይ በቀደምት መዋል አለመዋል ለማረጋገጥ የሚደረገውን ማጣራት (ቁጥጥር) ሊጨምር ይችላል የሚለውን ጠቅላላ ድንጋጌ የሚደግፍ ያደርገዋል፡፡ ይህ ሁኔታ እንዲሟላ በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ላይ ተጠይቋል፡፡ እንዲሁም በጥቅም ላይ መዋሉ በጣም የሚደገፍ ነው፡፡ ዕውቅና ማሰጠት የብሔር ማህበረሰቡን ልዩ መሆን ህዝብ እንዲያውቀው ከመርዳቱም በላይ ሌሎች ሰዎችና የመንግስት አካላት ልዩነቱን አውቀው እንዲያከብሩ ማስጠንቀቂያ ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህም በላይ ህግ እንደመሆኑ መጠን የመንግስት አስተዳደሮች የብሄር ማህበረሰብ መብቶችን በሚመለከቱበት ጊዜ ዋጋ ሊሰጡት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡

ስለሆነም እውቅና ይሰጠው የተባለው ማንነት በሃገሪቱ በየትኛውም ክፍል በሚገኝ መልክዓ ምድር ውስጥ የሰፈረ ማህበረሰብ እውቅና የተሰጠው ከሆነ ይህ እውቅና ያገኘው የብሔር ማህበረሰብ ከሰፈረበት መልክዓ ምድር ውጭ የሚገኝ ማናቸውም ማህበረሰብ ይህንኑ ማንነት እንዳለኝ እውቅና ይሰጠኝ ብሎ የሚያቀርበው የማንነት ጥያቄ ሊኖር አይችልም፡፡

ይህ ከሆነ፡ የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት ጥያቄ ብሎ ነገር እንዴት ሊቀርብ ይችላል? የአማራ የብሔር ማህበረሰብነት አስቀድሞ በህገመንግስቱ አንቀፅ 47/1/ /3/  ዕውቅና የተሰጠው ጉዳይ ነው፡፡ ህገመንግስቱ ከዚህ አልፎ የአማራ ብሔር ማህበረሰብ ክልል የመመስረት መብቱን ጥያቄ ማቅረብ ሳያስፈልገው በራሱ አክብሮታል፡፡ይህንንም የአማራ ክልል ከሚለው ስያሜ እና ከህገመንግስቱ አንቀፅ 47/2/ መሰረታዊ መንፈስና ይዘት መገንዘብ አዳጋች አይደለም፡፡ በዚህ መሰረት ህገመንግስቱ ከፀደቀበት ጊዜ አስንቶ እስከ አሁን የብሔር እውቅና አግኝቶ የብሔር መብቶችን በመጠየቅ እያጣጣመ ያለ የብሔር ማህበረሰብን ማንነት በሌላ ክልል ውስጥ በተከለለ መልክዓ ምድር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ መሰረት ዕውቅና ያገኘው ማንነትን ዕውቅና ይሰጠን ብለው ሊጠይቁ የሚያስችላቸው መብት የላቸውም፡፤

የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ፤ የጥያቄ አገላለፅ እንደሚያሳየው የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ዕውቅና ሊያሰጠው የሚችል ልዩ ማንነት የለውም፡፡የማንነት ጥያቄው ከጥያቄ አገላለፅ እንደሚያሳየው በወልቃይት መልክዓ ምድር ውስጥ የሰፈረ የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት እውቅና ይስጠው የምል ነው፤፤   የአንድ የማንነት ጥያቄ ዋና ተፈላጊ ባህርይ ልዩ መሆኑ ነው፡፡ የፌዴራሉ ህገመንግስት ይህን ዋና ተፈላጊ ባህርይ ጠያቂው አካል ያለው መሆን አለመሆኑን የሚለይበትን ደንብ በአንቀፅ 39/5/ ላይ አደራጅቷል፡፡

አንድ ማህበረሰብ ልዩ ያልሆነ የማንነት ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ይህ ማንነት ተፈላጊውን ልዩነት የማያሟላ በመሆኑ የማንነቱ ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ዕውቅና ሊሰጠው አይችልም፡፡ አንድ የማንነት ጥያቄ ልዩነቱን ያጣ ከሆነ ከመነሻው ሊቀርብ አይችልም፤ ከቀረበም ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡ ለዚህም ነው ጥያቄው በፅሑፍ መቅረብ አለበት እንዲሁም ፅሑፉ በአንቀፅ 39/5/ ላይ የተመለከቱት መስፈርቶች የተሟሉ መሆኑን በማሳየት መቅረብ ይገባዋል ተብሎ በስልጤ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወሰነው፡፡

በኢትዮጵያ ፌ.ዲ.ሪ ህገመንግስት መሰረት የብሔር ማንነት ጥያቄ (አቤቱታ) ማቅረብ መብት ያለው ማን ነው? እዚህ ላይ አንድ ወገን የማንነት ጠያቂ ሆኖ ለመቅረብ የሚጠይቀውን መመዘኛ አንስተን በሰፊው እንመለከታለን፡፡ በህገመንግስት አንቀፅ 39/5/፣ 62/3/ እና በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 19/1/ ላይ ጠያቂው ወገን ለጥያቄው መነሻ በሆነው ነገር ወይም ክሱ በተመሰረተበት ጉዳይ ላይ መብት ያለው ካልሆነ በስተቀር የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ ማቅረብ አይፈቀድለትም በማለት ተደንግ¹ል፡፡ የዚህ መርህ ጠቀሜታ አንድ መብት ከተጎናፀፈው ሰው በቀር ሌላ ሰው/ሰዎች ጥያቄ እንዳያቀርቡ ለማድረግ ነው፡፡

የዚህ መርህ ሌላኛው ጠቀሜታ የማንነት ጥያቄ ጉዳይ በተመለከተ ራሱ ባሉጉዳዩ ነው አቤት ማለት ያለበት መሆኑ ነው፡፡ በዚህም በአንድ ማንነት ጉዳይ ላይ ሁለት ጊዜ ጥያቄ እንዳያቀርብ ለማድረግ ይረዳል፡፡ የማንነት ጥያቄ የመብት ማስከበር ጉዳይ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ መብት ከመነሻው ከሌለው መብት ማስከበር ብሎ ነገር የለም፡፡ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ተወካዬች ነን ባዬች በምንም መልኩ የማንነት ጥያቄ የማቅረብ መብት የላቸውም፡፡የብሔራዊ ማንነት ጥያቄ የማቅረብ መብት የሌለው ወገን የማንነት ጥያቄ ከመነሻው እንዳያቀርብ ማድረጉ ቢያንስ ሁለት ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ አንደኛው መብት የሌለው ሰው መብቴ ይከበርልኝ ብሎ ቢጠይቅ የጊዜና የሃብት ብክነትን ከማስከተሉ በቀር በሂደቱ በስተመጨረሻ የሚጠይቀውን ዳኝነት በህገመንግስቱ በተቀመጠው መልክ ቅርፅ አግባብ ሊያገኘው አይችልም፡፡ የማንነት ጥያቄ ዕውቅና የማግኘት ጥያቄ ብቻ ነው፡፡ የጥያቄው መፍትሔ ሊሆን የሚችለው ዕውቅና መስጠት ወይም ዕውቅና መንፈግ ነው፡፡ ይህ በስተመጨረሻ የሚወሰን መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የማንነት ጥያቄ ጠያቂ ወገን ጥያቄ የሚያቀርብበት የጥያቄ ምክንያት ሊኖረው እንደሚገባ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ይሄ የጥያቄ ምክንያት የማንነት ጥያቄን አስመልክቶ በሚቀርበው ፅሑፍ (ማመልከቻ) ላይ ቢያንስ በፍሬ ነገር ረገድ ተዘርዝሮና ተብራርቶ መገለፅ ይኖርበታል፡፡ የማንነት ጥያቄ ማመልከቻ አመልካቹ መብቱን የሚጠብቅበትን በአጭሩ የያዘ መሆን አለበት፡፡ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 2/1/ ድንጋጌ መሰረት የማንነት ጥያቄን በሚመለከት በሚቀርብ ፅሑፍ ላይ የጥያቄው ይዘት በዝርዝር የሚያሳይ መሆን አለበት ወይም ዋና ዳኝነት የተጠየቀበትን ፍሬ ነገሮች በአጭሩ መገለፅ አለበት፡፡ ይህ ካልተገለፀ ጥያቄው ከመጀመሪያው ወደ ጥያቄው ፍሬ ጉዳይ ሳይገባ የጥያቄ ህጋዊ ምክንያት የለውም ተብሎ ውድቅ ሊደረግ ይገባል፡፡

በዚህም ራሱ ጠያቂው ወደ ጉዳዩ ዳኝነት ቢገባ የሚያባክነው ጊዜ፣ ጉልበትና ሃብት እንዲጠብቅ ያደርጋል፡፡ በሌላ በኩል የማንነት ጥያቅው የሚመለከተው ክልል መንግስት በእንዲህ አይነት ጥያቄ የተነሳ ከሚያባክነው ጊዜ፣ ጉልበትና ሃብት ተጠብቆ ጊዜውን ጉልበቱንና ሃብቱን በሙሉ በልማት ስራ ላይ እንዲያውለው ያስችላል፡፡ ሁለተኛ እንዲሁም ጉዳዩን የሚዳኘው አካል የጥያቄው መሰረት የሆነ መብት የሌለ መሆኑን ከማመልከቻው በሚገባ መረዳት በተቻለ ጊዜ ውድቅ ማድረግ ሲገባው ወደ ዋናው ጉዳይ በመግባት ሂደቱን በማስቀጠል ከወሰደው ጊዜ፣ ጉልበትና የህዝብ ሃብት ብክነት መጠበቅ ይቻላል፡:

ይህ ካልሆነ የህግ የበላይነት ሊሰፍን አይችልም፡፡ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር አደጋ ላይ ይወደወቃል ዕድገትም የሚታሰብ አይሆንም፡፡ የህግ የበላይነት (Rule of law) የሚሰፍነው ዜጎች፣ ቡድኖችና ባለስልጣናት ህጎችን ሲያከብሩ ነው፡፡ የህጎች መከበር ግለሰቦች ሆኑ ቡድኖች ለህግ ተገዥነታቸውና በህግም ፊት እኩል መታየታቸውን ያረጋግጣል እንዲሁም ማንም ሰው ወይም ቡድን ከህግ ውጭ በዘፈቀደ በባለስልጣኖችም በሆነ በሌሎች ግለሰቦች ወይም ቡድኖች መንገላታት እንዳይደርስበት/ እንዳይደርስባቸው ይከላከላል፡፡ ይህን ዓላማና ግብ መሰረት አድርጎ ነው ፍትህ የማግኘት መብት መቃኘት ያለበት፡፡ በዚህም አስተሳሰብ በቀላል ወጪ ጥራት ያለው ፍትሕ የማግኘትን መብት እውን ለማድረግ ይቻላል፡፡

እርግጥ ነው አንዳንድ ጊዜ ልዩ በሆኑና በህግ መጠበቅ ባላቸው ማንነቶችና ልዩ ባልሆኑ ማንነቶች መካከል ያለው መለያየት በጣም ግልፅ ባለመሆኑ ወይም መለያየቱን ባለመረዳት የወልቃይት ህዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ አስከትሏል፡፡ ህገመንግስቱ እንደሚለው በአንድ የማንነት ዕውቅና በማግኘት የብሔሩ መብቶች የመጠቀም መብትን የያዙት የብሔር መብቶች በህገመንግስቱ በተቀረፀላቸው ቅርፅ ልክ መሰረት ይተዳደራሉ፡፡ የማንነት ጥያቄ ጉዳዩችን የሚመለከት በአሁኑ ጊዜ ስራ ላይ የዋለ ዝርዝር የኢትዩጵያ ልዩ ህግ የለም፡፡እርግጥ ነው፤ የክልሎች ህገመንግስት በዚህ ረገድ መብት ካጎናፀፈ ሊጠይቁ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የኦሮሞ ማህበረሰብ በአማራ ክልል ውስጥ ዕውቅና ተሰጥቶት የራሱ የብሔረሰብ ዞን ያቋቋመው በፌዴራል ህገመንግስት መሰረት መብት ኖሮት ሳይሆን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ህገመንግስት በዚህ ረገድ ዕውቅና የሰጠው በመሆኑ ነው፡፡

ከዚህ ውጪ፤ አስቀድሞ ዕውቅና ያገኘን ና ልዩ  ያልሆኑ ማንነት ዕውቅና ይሰጠው ብሎ በሌላ ክልል ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ሊጠይቁ መብት የላቸውም፡፡ ይህም ክርክር ቢያንስ በአራት ህገመንግስታዊ መሰረቶች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ይኸውም፡-

የአንድ ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብ አቋም ለማግኘት ዋና ተፈላጊ ነገር ልዩ (distinctiveness) መሆኑ ነው፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገመንግስትና የክልሎች ህገመንግስት ይህን ተፈላጊ ነገር የያዙትንና ያልያዙትን ማህበረሰቦች የሚለዩ ደንቦችን አደራጅቷል፡፡ አንድ ማህበረሰብ ልዩ ያልሆነ የማንነት ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ይህ ማንነት ተፈላጊውን ልዩነት የማያሟላ በመሆኑ የማንነቱ ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ዕውቅና ሊሰጠው አይችልም፡፡ አንድ የማንነት ጥያቄ ልዩነቱን ያጣ ከሆነ ከመነሻው ሊቀርብ አይችልም፤ ከቀረበም ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም፡፡ ለዚህም ነው ጥያቄው በፅሑፍ መቅረብ አለበት እንዲሁም ፅሑፉ በአንቀፅ 39/5/ ላይ የተመለከቱት መስፈርቶች የተሟሉ መሆኑን በማሳየት መቅረብ ይገባዋል ተብሎ በስልጤ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወሰነው፡፡

ሁለተኛው ዕውቅና ይሰጠው የተባለው ማንነት ከዚህ ቀደም ዕውቅና ያልተሰጠው መሆን አለበት፡፡ ጥያቄው አስቀድሞ ዕውቅና ያገኘ የብሔር ማንነትን የሚመለከት በመሆኑ በድጋሚ ዕውቅና ሊሰጠው የማይገባ በመሆኑ ነው፡፡ ይህንንም ከቅማንትና ከስልጤ ጉዳዩች እና ውሳኔዎች መመልከት ይቻላል፡፡የስልጤና የቅማንት ብሄራዊ ማንነት ጥያቄዎችና አወሳሰናቸው ይህንኑ ያሳያል፡፡ በዚህም መሰረት የስልጤና የቅማንት ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብነት አቋም እውቅና አግኝተዋል፡፡የቅማንት ማህበረሰብ ሆነ የስልጤ ምህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብ ዕውቅና ይሰጠን በማለት ጥያቄ ያቀረቡት ከዚህ ጥያቄ በፊት የቅማንት ሆነ የስልጤ ማህበረሰብ የብሔር ማህበረሰብነት ዕውቅና ያላገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህ ሁለት የማንነት ጥያቄዎች መገንዘብ እንደሚቻለው የማንነት ጥያቄ ሊኖር የሚችለው ሆነ ተቀባይነት የሚኖረው የተጠየቀው የብሔር ማህበረሰብ ማንነት ከዚህ ቀደም እውቅና ያላገኘ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ አስቀድሞ የብሔር ማህበረሰብነት እውቅና ያገኘ ማንነት በድጋሚ እውቅና ይሰጠን ብሎ መጠየቅ ጨርሶ እንደማይቻል ከህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት በስልጤ እና በቅማንት ጉዳይ ከሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የደቡብና የአማራ ክልሎች በቅማንትና በስልጤ ጉዳይ ከሰጧቸው ውሳኔዎች እና ከእነዚህ ጥያቄዎች ባህርይ መረዳት ይቻላል፡፡

የብሔር መብቶች ከሰብአዊ መብቶች የሚለዩት የብሔር መብቶች ቡድናዊ (ማህበረስባዊ) መብቶች በመሆናቸው ነው፡፡ ሰብአዊ መብት ግን ግለሰባዊ ነው፡፡ የቡድን/የማህበረስብ  መብት ሲባል መብቱ በአንዴ በጋራ የሚሰራበት ማለት ነው፡፡  የህገመንግስቱ አንቀፅ 39/1/፣ /3/ እና /5/ እንደሚያስገነዝበው በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩና የብሔር ማህበረሰብ ባህርይ የሚያሳይ እያንዳንዱ የብሔር ማህበረሰብ በሰፈረው መልክዓ ምድር ውስጥ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት አለው፡፡ እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከኢትዮጵያ መነጠል ከፈለገ የሰፈረበትን መልክዓ ምድር ይዞ የመነጠል መብት አለው፡፡ ለዚህም ነው የህገመንግስቱ መግቢያ #እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ህዝቦች – – – የየራሳችን መልክዓ ምድር አሰፋፈር የነበረንና ያለን – – -; በማለት የተጠቀሰው፡፡

ከዚህ በላይ፤ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች መሰረት የብሔር መብቶች የድንበር ባህርይ አላቸው ማለትም በድንበር የተወሰኑ (territorial approach to ethnic rights) ናቸው፡፡ የወልቃይት መልክዓ ምድር ውስጥ የሰፈረው ህዝብ በህገመንግስቱ አንቀፅ 39 /3//5/ እና 46/2/ መሰረት የትግራይ ማንነት ባህርይ የሚያሣይ መሆኑ ታምኖበት ከሽግግር ዘመኑ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ለግማሽ ክፍለ ዘመን በትግራይ ክልል ውስጥ ተከልሎ የሚገኝ ምድር ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ክልል ውስጥ የሚገኙ የአማራ ተወላጆች በፌዴራሉ ህገመንግስት ሆነ በትግራይ ህገመንግስት መሰረት የአማራ ማንነት እውቅና ይሰጠን ብለው የመጠየቅ ህገመንግስታዊ መብት የላቸውም፡፡ ዕውቅና የማግኘት መብት የሌላቸው በመሆኑ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኙት የአማራ ብሔር መብቶች ሊኖሩ አይችሉም፤በትግራይ ክልል ውስጥ  የሚጠቀሙበትም የአማራ ብሔር መብቶች የሉም፡፡

የብሄር መብቶች በብሄሩ መልክዓ ምድር ወይም ክልል የተወሰኑ ናቸው፡፡ የብሄር የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት እስከመገንጠል ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ዕውቅና የተሰጠው በሽግግሩ ቻርተር ነው፡፡ የብሄሮችን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል ተቋማዊ ለማድረግ ሲባል በሽግግር ጊዜ በወጣው አዋጅ ቁጥር 7/1992 አማካኝነት ብሄሮች የየራሳቸውን ክልል በሰፈሩበት መልክዓ ምድር ወሰን ውስጥ ሊመሰርቱ እንደሚችሉ ተደንግ¹ል፡፡ ይህም ማለት ክልሎች የሚደራደሩት በዋናነት በማንነት ላይ ነው ማለት ነው፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገመንግስትም ከቻርተሩ ጋር ተመሳሳይ የሆነ አቋም ይዟል፡፡ የኢትዩጵያ ፌዴራሊዝም ብሄር ተኮር ፌዴራሊዝም ነው የሚባለውም ክልሎች የሚደራጁት በማንነት ላይ በመሆኑ ነው፡፡ ይኸውም በህገመንግስቱ አንቀፅ 47/1/ እና 47/2/ ላይ ተመልክቷል፡፡አንቀፅ 47/1/ ዘጠኝ ክልሎች የጠቀሰ ሲሆን እነዚህም ትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች፣ የሀረሪ ሕዝብ ክልል እና የጋምቤላ ክልል ናቸው፡፡ የክልሎች ስያሜ ስለ ክልሎች የብሔር ስብጥር ከወዲሁ ይጠቁማል፡፡

አንቀፅ 47/1/፣ /2/፣ /3/፣ /4/፣ /6/ እና /9/ እንደሚያሳዩት ትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሶማሌ እና ሐረሪ ህዝቦች የየራሳቸው ክልል አላቸው፡፡ ትግራዊያን የትግራይ ብሄር መብቶች በትግራይ ክልል ውስጥ ይጠቀማሉ፣ አፋሮች ደግሞ በአፋር ክልል ውስጥ ያከናውናሉ፣ አማራዎች ደግሞ በአማራ ክልል ውስጥ ይሰሩበታል፣ ኦሮሞዎችም እንዲሁ በኦሮሞ ክልል ውስጥ ይሰሩበታል፣ ሱማሌዎችም በተመሳሳይ በሱማሌ ክልል ውስጥ እንዲሁም ሐረሪዎች በሐረሪ ክልል ውስጥ ብሔራዊ መብቶቻቸውን ያራምዳሉ፡፡

ህገመንግስቱ የብሄር መብቶች ክልል በመመስረት በበለጠ የሚጠበቁበትን ዘዴ ተነድፏል፡፡ ይህንንም ከህገመንግስቱ አንቀፅ 47/1/ ላይ መረዳት ይቻላል፡፡ ይኸውም ድንጋጌ ክልል ያልመሰረቱ ብሔሮች በማናቸውም ጊዜ ከፈለጉ ክልል የማቋቋም መብት እንዳላቸው ደንግ¹ል፡፡ ይህን ድንጋጌ ከመገንጠል መብትና ራስን በራስ ከማስተዳደር መብት ጋር በጋራ ስንመረምረው ማንኛውም ዕውቅና የተሰጠው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ በኢትዩጵያ ስር የራሱን ክልል በሰፈረበት መልክዓ ምድር የማቋቋም መብት እንዲሁም የሰፈረበትን መልክዓ ምድር እንደያዘ የመገንጠል መብት እንዳለው መገንዘብ የሚቻል ይሆናል፡፡ በዚህም ብሔሩ የሰፈረበት መልክዓ ምድር ወይም ብሔሩ ከመሰረተው ወይም ካለው ክልል ወሰን ጋር በጥብቅ የተቆራኙ ናቸው፡፡

አንቀፅ 39 ስለ ቋንቋ፣ ባህል እና ራስን በራስ ስለማስተዳደር መብቶች ደንግ¹ል፡፡ እነዚህ መብቶች የብሄር የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብቱ አካል ናቸው፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት እነዚህ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት አካል የሆኑ መብቶች በድንበር ወሰን ዘዴ (territorial approach mechanism) ተግባራዊ እንዲደረግ ይፈለጋል፡፡ ይሁንና አንቀፅ 39 በተጨማሪ የብሄር ቡድኖች በክልል እና በፌዴራል አስተዳደሮች ውስጥ ሚዛናዊ ውክልና የማግኘት መብት እንዳላቸውና ይህም መብት የብሔር የራሱ በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት አካል መሆኑን ደንግ¹ል፡፡ ይህ ሚዛናዊ ውክልና የብሔር ማህበረሰቦች በክልልና በፌዴራል አስተዳደሮች ውሳኔዎች ውስጥ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ እንዲሁም በብሔር ማህበረሰቦች መካከል አንድነትን ለማጠናከር ዕድልን ይፈጥራል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት የውክልና ዋስትናን በተመለከተ የያዘው ጥቂት ድንጋጌዎች ብቻ ነው፡፡ የፌዴራሉ መንግስት ምክር ቤቶች ሁለት ሲሆኑ እነዚህም የህዝብ ተወካዩች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ናቸው፡፡ የህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት አባላት የመላው የኢትዩጵያ ህዝብ ተወካዩች ሲሆኑ እነሱም የሚመረጡት በየአምስት ዓመቱ ሆኖ ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ ሆነና ድምፅ ሚስጢር ሚሰጥበት ስርዓት ነው፡፡ በሌላ በኩል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት የኢትዩጵያ የብሔር ማህበረሰቦች ተወካዩች ስብስብ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ የኢትዮጵያና የብሔር ማህበረሰብ ቢያንስ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውስጥ አንድ ተወካይ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም የብሔር ማህበረሰቡ አንድ ሚሊዩን ህዝብ አንድ ተጨማሪ ወኪል ይኖረዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት 112 ሲሆኑ እነዚህ አባላት 69 የተለያዩ የኢትዮጵያ የብሔር ማህበረሰቦችን የወከሉ ናቸው፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በክልል ምክር ቤት ይመረጣሉ ወይም የክልል ምክር ቤቱ የብሔር ማህበረሰቡ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ተወካዩች በቀጥታ በህዝቡ እንዲመረጡ ከወሰነ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የብሔር ማህበረሰቡ ተወካዩች በብሔር ማህበረሰቡ በቀጥታ ይመረጣሉ፡፡ እስከ አሁን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በክልል ምክር ቤት የሚመረጡበት አሰራር የሰፈረና አንድ ጊዜ ከልል እስከአሁን የብሄር ማህበረሰቡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በብሄር ማህበረሰቡ እንዲመረጡ የወሰነበትና ያደረገበት ሁኔታ የለም፡፡

እዚህ ላይ እስከአሁን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ስብስብ ዝርዝርን ስንመረምረው የብሔራዊ ልዩነት ድንበራዊ አቋም ወይም ዘዴ ሃይል መልሶ ይመጣል፡፡ የብሔር ማህበረሰቦችን ከተወሰነ መልክዓ ምድር ጋር የተቆላለፈ ወይም የተቆራኘ በመሆኑ በብሄር ማህበረሰብና በግዛት መካከል ማህበር (ህብረት) አለ፡፡ ስለዚህ የእያንዳንዱ የኢትዮጵያ የብሔር ማህበረሰብ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ተወካይ የብሔር ማህበረሰቡ ከሰፈረበት መልክዓ ምድር የሚመረጡ መሆኑ አመክዩአዊ ነው፡፡ ነገሩን በምሳሌ ለማሳየት ያህል የአማራ ብሄረሰብ የራሱ የሆነ ክልል ያቋቋመ በመሆኑ የአማራ ብሔረሰብ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ተወካዩች በክልሉ ምክር ቤት የሚመረጡት ከአማራ ክልል ነው፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ዝርዝር እንደሚያሳየው ሁሉም 114 የአማራ ብሔር ማህበረሰብ ተወካዩች የተመረጡት ከአማራ ብሔራዊ ክልል ነው፡፡ ብዙ የአማራ ብሔር ማህበረሰብ ተወላጆች ከአማራ ክልል ውጪ እንደሚኖሩ ይታወቃሉ ለምሳሌ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ይኖራሉ፡፡ ይሁንና የኦሮሚያ ክልል በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ብሔር ተወላጆችን በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚወከሉ ሰዎች ልኮ አያውቅም፡፡ በመሆኑም በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚወከሉት በአማራ ክልል ምክር ቤት በተመረጡ የአማራ ተወካዩች ነው፡፡ ኦሮሞ ብሄር ማህበረሰብም ተመሳሳይ ነው፡፡ በፌዴሬሽን ምክር ቤት 20 የኦሮሞ ብሄር ተወካዩች ያሉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አስራ ዘጠኙ በኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት የተመረጡ ናቸው፡፡ አንደኛው የኦሮሞ ብሄር ተወካይ ደግሞ በአማራ ክልል ምክር ቤት የተመረጠ ነው፡፡ አንድ የኦሮሞ ተወካይ በአማራ ክልል ምክር ቤት መመረጡ ከብሔራዊ ልዩነት የድንበር ወሰንተኝነት ዘዴ/አቋም ማፈንገጥ አይደም፡፡ ይልቁንም ይህንኑ ዘዴ/አቋም የሚያጠናክር ነው፡፡ የኦሮሞ ብሔር ማህበረሰብ የራሱ ክልል ብቻ ያለው ሳይሆን የኦሮሞ ብሄር በአማራ ክልል ውስጥ የራሱ የሆነ የብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አለው፡፡ ይህም ማለት ኦሮሞ የራሱን እድል በራሱ የመወሰን መብቱን በኦሮሚያ ክልል እና በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ውስጥ የመጠቀም መብት አለው ማለት ነው፡፡ የብሄር ማህበረሰብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚወከለው በብሄሩ መልክዓ ምድር ወሰን መስፈርት መሆኑን በክልል መንግስታት (አስተዳደር) ደረጃም ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ ከዚህ በላይ በተመለከትናቸው የብሔራዊ ልዩነት ህገመንግስታዊ ማዕቀፎች በሙሉ መልክዓ ምድራዊ አቋም (ዘዴ) ላይ የተመሰረቱ መሆናቸውን በግልፅ መገንዘብ ይቻላል፡፡

በጠቅላላው ብሔራዊ ማንነት ጥያቄ ደንቦች ቢያንስ ሁለት ጠቅላላ (general) መለኪያዎች እንዲሟሉ ይጠይቃሉ፡፡ የማንነት ጥያቄ መለኪያዎች ውስጥ አንደኛው ጥያቄ አቅራቢው አካል ለጥያቄው ምክንያት የሚሆን መብት ሊኖረው ይገባል፡፡ ምክንያቱም ጥያቄው የመብት ማስከበር ጥያቄ በመሆኑ የሚከበርለት መብት ሊኖረው ግድ ይላል፡፡ መብት (right) ማለት ደግሞ የህግ ጥበቃ የተደረገለት ጥቅም (legal right) ማለት ነው (አንቀፅ ህገመንግስት 39/5/) ፡፡ዕውቅና ይሰጠው የተባለው ብሔራዊ  ማንነት በዝህ ጠቅላላ (general) መለኪያ ስነጠር ልዩነት(distinctiveness) ካሳየ ዕውቅና ይሰጠዋል፡፡ ሁለተኛው መለኪያ ደግሞ ዕውቅና ይሰጠው የተባለው ብሔራዊ ማንነት ከዚህ ቀደም ዕውቅና ያልተሰጠው መሆን አለበት፡፡ ጥያቄው አስቀድሞ ዕውቅና ያገኘ የብሔር ማንነትን የሚመለከት በመሆኑ በድጋሚ ዕውቅና ሊሰጠው የማይገባ በመሆኑ ነው፡፡ ይህንንም ከቅማንትና ከስልጤ ጉዳዩች እና ውሳኔዎች መመልከት ይቻላል፡፡

1.2 ስለ ብሄር ማንነት ዕውቅና ውጤት    

አንድ ማህበረሰብ በህገመንግስቱ የተጠቀሱትን የብሔር መብቶች ልጠቀም ወይም በስራ ላይ ይዋልልኝ ብሎ ከመጠየቁ በፊት የማህበረሰቡ ልዩነት ዕውቅና እንዲያገኝ ማድረግ በቅድሚያ ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም በህገመንግስቱ ከአንቀፅ 39/1/ እስከ 39/4/ የተጠቀሱት መብቶች ባለቤት የብሔር ማህበረሰብ በመሆኑ ነው፡፡ በእነዚህ የብሔር ማህበረሰቦች መጠቀም ሲችሉ የብሔር ማህበረሰብ ዕውቅና ያላቸው ማህበረሰቦች ደግሞ በእነዚህ የብሔር መብቶች ጨርሶ ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡

ስለሆነም በኢትዩጵያ ውስጥ አንድን ማህበረሰብ በብሔር መብቶች ከመጠቀሙ በፊት ብሔራዊ ልዩነቱን ዕውቅና እንዲያሰጥ የሚያዝ ህግ አለ፡፡ ይኸውም በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ነው፡፡ እንደሁም በአዋጅ ቀትር 251/1993 አንቀፅ 19 ላይ ተመልክተል፡፡ከዚህም በላይ፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በስልጤ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ላይም  ተወሰነል፡፡የብሔራዊ ልዩነት ዕውቅና ማግኘት የሚያስከትለውን ህጋዊ ውጤት የሚናገር ሕግ ያለ በመሆኑ ዕውቅና ማግኘቱ ሕጋዊ ውጤትን ያስከትላል፡፡ በመሆኑም ዕውቅና ማግኘት የሚሰጠው ህጋዊ አገልግሎት አለ፡፡ ሆኖም ዕውቅና ማግኘቱ የሚያስከትለውን ህጋዊ ውጤት በመወሰን ረገድ ሊኖር የሚችለውን ችግር የሚመለከታቸው የክልልና የፌዴራል አስተዳደሮች ሊመለከቱት የሚያስፈልግ ይመስላል፡፡ በዚህም የህጋዊ ውጤቱን ወሰን አመለሸጋ በሆነ ዘዴ አስቀድሞ ለመፍታት የሚቻልበትን ሁኔታ መፍጠር የሚቻል ይመስላል፡፡

አንድ ዕውቅና ያገኘ ልዩነት የሚያስከትለው ህጋዊ ውጤት የህብረት (የጋራ) የብሄር መብቶችን ነው፡፡ ብሔራዊ ልዩነቱ ዕውቅና ማግኘቱ የሚያስከትለው ህጋዊ ውጤት አንድ የጋራ የብሔር ማህበረሰብን መብቶች ነው፡፡ ዕውቅናውም የሚያስከትለው ህጋዊ ውጤት በመልክዓ ምድራዊ ወሰን ይኖረዋል፡፡ ወሰኑም ዕውቅና ያገኘው የብሄር ማህበረሰብ የሰፈረበት መልክዓ ምድር ነው፡፡ እንዲሁም የማንነት ጥያቄ ዕውቅና ማግኘቱ ዕውቅና ያገኘው ማህበረሰብ የክልል ወሰን አከላለል ለውጥ ጥያቄ የማቅረብ መብትን አያስከትልም፡፡ ይህንንም ከአንቀፅ 48 አወቃቀር፣ ድንጋጌ እንዲሁም ከአንቀፅ 39 በሚገባ መረዳት የሚቻል ይመስላል፡፡

1.3 ስለብሄር ማህበረሰብ አባልነት

የብሄር ማህበረሰብ አባልነት ማግኛ/መወስኛ መንገድ ምንድን ነው? የብሄር ማህበረሰብ አባልነት ከተገኘ በሃላ መቀየር/መለወጥ ይቻላል ወይ?የሚሉትን ነጥቦች በተመለከተ ጥቂት እንላለን፡፡ ማህበረሰብ የሚጀምረው ከብሄር ተወላጀነት ነው፡፡ ተወላጀነት የማህበረሰብ ዘር መፍለቅያ ነው፡፡ጥብቅ ተወላጃዊ ግንኙነት ያለበት ማህበረሰብ የማህበረሰቡን ባህል፤ቋንቋና ሃይማኖት ይጠብቃል እንዲሁም ያስጠብቃል፡፡

ማህበረሰብ ያለ ብሄሩ ተወላጀ ሊኖር አይችልም፡፡በሌላ አነጋገር የብሄር ተወላጀነት የሌለ እንደሆነ የብሄር ማህበረሰብ አይኖርም፡፡ስለዚህ ማህበረሰቡና መንግስት የብሄር ተወላጀነት የሚጠብቁበት አበይት ምክንያቶች እነዚሁ ናቸው፡፡

የብሄር ማህበረሰብ አባልነት ማግኛ/መወስኛ መንገዶች የሚከተሉት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡እነዚህም-    

(1) አንደኛው በትውልድ/በደም ነው፡፡ በዚህ መስረት በትውልድ/በደም የብሄር ማህበረሰብ አባልነትን ማግኘት ይቻላል ማለት ነው፡፡ (2) በመቀባትም ማግኘት ይቻላል፡፡ (3) ከምርጫም የብሄር ማህበረሰብ አባልነትን ማግኘት ይቻል ይሆናል፡፡ (4) በትውልድ ስፍራ የብሄር ማህበረሰብ አባልነትን ማግኘት ይቻል ይሆናል፡፡ (5) በምንባርም የብሄር ማህበረሰብ አባልነትን ማግኘት ይቻል ይሆናል፡፡ (6) በቋንቋ አንድ ሰው የብሄር ማህበረሰብ አባልነትን ማግኘት ይችል ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስትም ሆነ ሌላ የኢትዩጵያ ህግ የብሄር ማህበረሰብ አባልነት ማግኛ/መወስኛ መንገዶች በጣም ግልፅ በሆነ ሁኔታ አይገልፁም፡፡ህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ላይ የሚደነግገው ስለብሄር ማህበረሰብ አቁም ማግኛ መንገድ ነው፡፡        ይሁንና የብሄር ማህበረሰብ አባልነት ማግኛ/መወስኛ መንገድ ላይ የተወስነ ብርሃን ይፋነጥቃል፡፡  በልምድ እንደሚታየው የብሄር ማህበረሰብ አባልነት በምርጫና በደም ላይ የተመሳረተ ነው፡፡  የብሄር ማህበረሰብ አባልነት አንዴ ከተገኘ በሃላ መቀየር/መለወጥ የሚቻል መሆን/አለመሆኑን የኢትዮጵያ ሕገ መንግስትም ሆነ ሌላ የኢትዩጵያ ህግ በግልፅ አያሳዩም፡፡ የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄን በተመለከተ የወልቃይት ማህበረሰብ ስለ ማንነቱ በ1984 ና በ1999 አ.ም በተደረጉት ህዝብና ቤቶች ቆጠራዎች ገልጡዋል፡፡እንድሁም በሌሎች መንግስታዊ ስነዶች በተለይም በቀበሌ መታወዊያ ላይ ገልጠዋል፡፡ የወልቃይት ማህበረሰብ በመንግስታዊ ስነዶች ላይ የገልጠውን ማንነት(የብሄር ማህበረሰብ አባልነት) መቀየር/መለወጥ ይችላል ወይ?የሚለው ነጥብ በሚገባ መመርመር አለበት፡፡እንደጸሃፈው እምነት የብሄር ማህበረሰብ አባልነት አንዴ ከተገኘ በሃላ መቀየር/መለወጥ አይገባም፡፡የወልቃይት ማህበረሰብ በመንግስታዊ ስነዶች ላይ የገልጠውን ማንነት(የብሄር ማህበረሰብ አባልነት) በመመርመር ማንነታቸውን(የብሄር ማህበረሰብ አባልነታቸውን) በተመለከተ መመርመር ያስፋልጋል፡፡

2. የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ

2.1 የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ ባህርይና ጥያቄውን የማቅረብ መብት

የክልሎች ወሰን ለውጥጥያቄ ምንድ ነው? ጥያቄውን የማንሳት መብት ያለው ማን ነው? ህጉስ እንዴት ነው የሚጠበቀው? የዚህ ክፍል ዓላማ እነዚህን ጥያቄዎችና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚመለከቱትን ህገመንግታዊና ሌሎች የበታች ህጎች በመመርመር (በመዳሰስ) ምላሽ መስጠት ነው፡፡

የዚህ ጥያቄ (አቤቱታ) መሰረትና ምንጭ በህገመንግስቱና በአዋጅ ቁጥር 251/1993 ላይ ተደንግ¹ል፡፡ ህገ መንግስቱ በአንቀፅ 48/2/ ላይ ክልሎች የክልል ወሰን ለውጥ ጥያቄ (አቤቱታ) የማቅረብ መብት እንዳላቸው ደንግ¹ል፡፡ እርግጥ ነው የዚህ ድንጋጌ መሰረት የህገመንግስቱ አንቀፅ 39/1/ እና /3/ እንዲሁም 46/2/ መሆናቸውን መረዳት ከባድ አይደለም፡፡ አዋጅ ቁጥር 251/1993 ደግሞ በአንቀፅ 27፣ 28፣ 29፣ 30 እና 31 ላይ ከዚህ በላይ የተደነገጉትን ህገመንግስታዊ መርሆዎችን ገቢራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የተባሉ ዝርዝር ጉዳዮች ደንግጓል፡፡

በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/1/ /3/ የተጠቀሰው እያንዳንዱ ብሄር በሰፈረበት መልክዓ ምድር ውስጥ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መንጠል መብቱ ተግባራዊ ለማድረግ እና ተቋማዊ ቅርፅ ለመስጠት ብሔሩ የሰፈረበት መልክዓ ምድር በክልል ደረጃ ማካለል ያስፈልጋል፡፡ በህገመንግስቱ ቃለ ጉባኤ ላይ እንደተመለከተው ለዘመናት በሃገሪቱ የደረሰው የህዝቦች አመፅ የሚያመላክተው ብሔር፣ ብርሔረሰቦች ራሳቸውን በራሳቸው ለማስተዳደር ባላቸው ፍላጎት ያደረጉት የመብት ማስከበር እንቅስቃሴ በመሆኑ ይህን ግምት ውስጥ በማስገባት በቋንቋ፣ በባህል እና በስነልቦና አመለካከት ቀረቤታ ያላቸውን በአንድ ክልል ስር እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል በሚል አስተሳሰብ መሰረት የክልል አከላለል በዋናነት በማንነት ላይ እንዲመሰረት ተደር¹ል፡፡ በዚህ የተነሳ በቅድሚያ በህገመንግስቱ አንቀፅ 39(3)(5) እና 46(2) መሰረት የክልሎች ወሰን ይካለላል፡፡ ከዚህ በኃላ የክልሎች ውስጥ ለውስጥ ጥያቄ በተነሳበት ጊዜ በህገመንግስቱ አንቀፅ 48/2/ መሰረት ጥያቄው ምላሽ ያገኛል፡፡

የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ (አቤቱታ) አግባብነት ያላቸው ህጎች ሁለት ናቸው፡፡ አንደኛው በህገመንግስቱ አንቀፅ 488() የተደነገገው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ ከአንቀፅ 23 -31 ድረስ የተደነገጉት ናቸው፡፡ እነዚህም የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ (አቤቱታ)  ጥያቄ ህጋዊ መሰረት ምንጭ ናቸው፡፡ በፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 48/2/ የሚደነግገው በአጎራባች ክልሎች መካከል የሚነሳ የወሰን ክርክር ስለሚፈታበት ዲሞክራሲያዊ መንገድ ነው፡፡ በክልሎች መካከል የወሰን ለውጥ ጥያቄ በተነሳበት ጊዜ ጥያቄው በቅድሚያ መፍትሔ የሚሰጠው የሚመለከታቸው ክልሎች በሚያደርጉት ስምምነት እንደሆነ በህገመንግስቱ አንቀፅ 48/2/ ላይ ተደንግ¹ል፡፡ እንዲሁም በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 23 ፤24 ፤25 እና ከ27 እስከ 31 ድረስ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

እነዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክልሎች በጥያቄው አፈታት ላይ መስማማት ካልቻሉ አንዱ ወይም ሁለቱ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክልሎች ጉዳዩን ለፌዴሬሽን ም/ቤት ዘንድ በማቅረብ መፍትሔ ሊሹ ይችላሉ፡፡ እዚህ ላይ የክልሎች ወሰን ጥያቄ ሊያነሳ (ሊያቀርብ) የሚችለው ማን ነው? የሚለውን አግባብነት ካላቸው የህግ ድንጋጌዎች አኳያ በጥሞና መመርመር የሚያስፈልግ ይመስላል፡፡

የህገመንግስቱ አንቀፅ 48/1/ እንዲህ ይላል፡- ‹‹የክልሎችን ወሰን በሚመለከት ጥያቄ የተነሳ እንደሆነ ጉዳዩ በሚመለከታቻዉ ክልሎች ስምምነት ይፈጸማል፡፡ የሚመለከታቸዉ ክልሎች መስማማት ካልቻሉ የፌዴሬሽኑ ም/ቤት የህዝብን አሰፋፈርና ፍላጎት በማድረግ ይወስናል››፡፡ እንዲሁም አንቀፅ 48/2/ ደግሞ በአንቀጽ 48(1) መሰረት ለፌዴሬሽን ም/ቤቱ የቀረበዉ ጉዳይ ከሁለት አመት ባልበለጠ ጊዜ ዉስጥ በፌዴሬሽኑ ም/ቤቱ የመጨረሻ ዉሳኔ ይሰጥበታል በማለት ደንግጓል፡፡.የእነዚህ ድንጋጌዎች ቋንቋ (language or wording) የሚያሳየው የክልሎች ወሰን ጥያቄ (ክርክር) የማቅረብ መብት ያላቸው ክልሎች መሆናቸውን መረዳት የሚቻል ይመስላል፡፡

እንዲሁም የእነዚህ ድንጋጌዎች አወቃቀር(structure of the provisions) እንደሚያስግነዝበው የክልሎች ወሰን ጥያቄ (ክርክር) የማቅረብ መብት ያላቸው ክልሎች መሆናቸውን መረዳት የሚቻል ይመስላል፡፡ አንቀፅ 48 የተዋቀረው በህገመንግስቱ ምዕራፍ አራት ውስጥ ሲሆን የዚህ ምዕራፍ አርዕስት የመንግስት አወቃቀር ይላል፡፡ የህገመንግስቱ ምዕራፍ አራት ከአንቀፅ 45 እስከ 49 ድረስ የተደነገጉትን ድንጋጌዎች የሚያቅፍ ሲሆን እነዚህም ድንጋጌዎች ስለ ስርዓተ መንግስት (አንቀፅ 45)፣ ስለ ፌዴራል ክልሎች (አንቀፅ 46)፣ ስለ ፌዴራል መንግስት (አንቀፅ 47)፣ ስለ አከላለል ለውጦች  (አንቀፅ 48) እና ስለ ርእሰ ከተማ (አንቀፅ 49) የሚደነግጉት ናቸው፡፡ በዚህ አወቃቀር መሰረትም የድንበር ወዝግብ ጥያቄ ተነሳ የሚባለው የፌዴራሉ መንግስት አካል የሆነ ክልል የክልል ወሰን ጥያቄ ባነሳ ጊዜ ነው፡፡ የድንበር ይገባኛል ጥያቄ ካለ አግባብ ባለው መንገድ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የመፍትሔ አሰጣጥ ስነ ስርዓት ተከትሎ መጠየቅ ይገባል፡፡ ይህንን በሚያጠናክር መልኩ ጥቅምት 18 ቀን 1987 ዓ.ም በተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የህገመንግስት ረቂቅ አጭር ማብራሪያ የወሰን ክርክር ጥያቄ የማቅረብ መብት ያላቸው ክልሎች መሆናቸውን ገልፃል፡፡

ከዚህ ባሻገር፡ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 27 ላይ እንደተመለከተው የክልሎች ወሰን ክርክር ሊኖር የሚችለው በክልሎች መካከል እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ የአዋጅ ቁጥር 251/1993 በክፍል አራት ውስጥ በክልሎች መካከል ወይም በክልልና በፌዴራል መንግስት መካከል የሚፈጠር አለመግባባት ስለሚፈታበት ሁኔታ ተደንግ¹ል፡፡ በጠቅላላው ክፍል አራት ስር የተደነገገው በክልሎች ወይም በፌዴራል መንግስትና በክልል መካከል በሚፈጠሩ አለመግባባቶች አፈታት ረገድ መሆኑን ከአዋጁ አንቀፅ 23፣ 24፣ 25 እና 26 ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ አዋጁ ከአንቀፅ 27 እስከ 31 ድረስ ደግሞ የድንበር ውዝግብ ስለሚፈታበት አግባብ ደንግ¹ል፡፡ ከእነዚህ ድንጋጌዎች መገንዘብ እንደሚቻለው የክልሎች ድንበር ወሰን ጥያቄ የማቅረብ መብት ያላቸው ክልሎች ናቸው፡፡በተጨማረ በፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 62/6/ ላይ በክልሎች መካከል የሚነሱ ክርክሮች በክልሎቹ ያልተፈታ እንደሆነ የፌዴሬሽኑ ም/ቤቱ ክርክሮቹን የመፍታት ስልጣን አለው፡፡ በክልሎች መካከል ከሚነሱ ክርክሮች መካከል አንዱ በፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 48 ላይ የተደነገገው በክልሎች የወሰን ለውጥ ጥያቄ ነው፡፡ ጥቅምት 18 ቀን 1987 ዓ.ም በተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የህገመንግስት ረቂቅ አጭር ማብራሪያ ገጽ 117 ላይ ስለ ፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 62/6/ ሲያብራራ በአንቀፅ 48፤51/6/ እና 51(17) ላይ የተደነገጉት አለመግባባቶችን የፌዴሬሽኑ ምክር ቤቱ የመፍታት ስልጣን ያለው መሆኑን፤ እንዲሁም ተከራካርዎቹ  ክልሎች መሆናቸውን አመልክቷል፡፡

እዚህ ላይ ልምዱንም መመልከት አስፈላጊ ይመስላል፡፡ የፌዴሬሽኑ ምክር ቤቱ በወንዶ-ገነትና አንገረ-ደደሳች ከተወስኑት ጉዳዩች የተወስኑት ናቸው፡፡ እነዚህም ጉዳዩች አንድ በአንድ ብንመለከት የክርክሩ አካል የነበሩት ክልሎች መሆናቸውን እንዲሁም የክልሎች ድንበር ለውጥ ጥያቄ የቀረበ በክልሎች መሆናቸውን መገንዘብ እንችላለን፡፡ በመሆኑም በትግራይ ወልቃይት ውስጥ የሚኖሩ አማራዎች በህገመንግስቱ አንቀፅ 48/2/ የተቀመጠውን የክልሎች ድንበር (ወሰን) ለውጥ ጥያቄ የማቅረብ መብት የላቸውም፡፡

ከዚህ ባሻገር፤ ክርክሬን የሚያጠናክር ሌላ መከራከሪያ ላቅርብ፡፡ የፌዴራል ህገመንግስቱ አንቀፅ 50/3/ እንደሚያስገነዝበው የክልል ከፍተኛ የስልጣን አካል የክልሉ ምክር ቤት ነው፡፡ እንዲሁም ተጠሪነቱም ለወከለው ክልል ህዝብ ነው፡፡ የክልል ስልጣን የሚያዘው በክልሉ ህዝብ ዲሞክራሲያዊና ቀጥተኛ ምርጫ ነው፡፡ ዲሞክራሲ የህዝብ መንግስት ነው፡፡ በዲሞክራሲ ህዝቡ የሚተዳደርበትን ህግ የራሱ ወኪሎች በግልፅና በሙሉ ነፃነት ተወያይተው የሚያወጡት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የክልል መንግስት ማለት የክልሉን ህዝብ መሰረታዊ አቋሞች፣ አንድነትና ነፃነት ከጣልቃ ገብ የሚከላከል፣ የክልሉን ህዝብ ደህንነት፣ አንድነትና መሻሻል የሚመራ፣ ህዝቡ ከውስጥ እርስ በራሱ ያለውን ግንኙነት፣ መብትና ግዴታ በህጋዊነት መርህ እየወሰነ የስልጣን ባለአደራ ሆኖ የሚያስተዳድር ተቋም ነው፡፡ በአጠቃላይ የክልሉ ህዝብ በማናቸውም መንገድ ወኪል ነው፡፡ በመሆኑም በአማራ ክልል የሚኖር የአማራ የብሔር ማህበረሰብ የክልል ወሰን ጥያቄ ካለው ጥያቄው በመንግስቱ አማካኝነት ሊቀርብ ይገባል፡፡

በጠቅላላው ጉዳዩ/ጥያቄው የክልሎች ወሰን ለውጥን የተመለከተ በሆነ ግዜ የወሰን ክርክር ሊቀርብ የሚችለው በክልሎች አማካኝነት ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም የወልቃይት ነዋሪ የሆኑ የተወሰኑ ሰዎች የአማራ ብሔር አባላት ነን በሚል የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ ለማቅረብ መብቱ የላቸውም፡፡

2.2 የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ (የድንበር ዉዝግብ) የሚፈታበት መንገድ

የክልሎች ወሰን ለውጥ ጥያቄ የሚፈታበት መንገድ አምስት ናቸው፡፡ እነዚህም፡- አንደኛው ዓይነት መንገድ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 28/1/ ላይ ተደንግ¹ል፡፡ ይኸውም ምክር ቤት የህዝብን አሰፋፈር በማጥናት አከባቢው ወደ የትኛው ክልል መካለል እንዳለበት ለመወሰን ሚያስችል በቂ መረጃ እንዳለው ካመነ በዚያው መሰረት ይወሰናል፡፡ በአዋጁ አንቀፅ 2/3/ እና 28/1/ መሰረት በዚህ ረገድ የመወሰን ስልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ ክልሎች እንዲህ አይነት ጥያቄን ተቀብለው የማስተናገድ ስልጣን የላቸውም፡፡ ምክንያቱም ማንም ሰው ወይም መንግስት በራሱ ጉዳይ ላይ መወሰን አይገባውም ከሚል መርህ ነው፡፡

ሁለተኛው ዓይነት መንገድ ደግሞ ህዝበ ውሳኔ ነው፡፡ የአዋጁ አንቀፅ 28/2/ እንደሚያስገነዝበው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያለህዝበ ውሳኔ የህዝቡን አሰፋፈር በማጥናት አከራካሪው አከባቢ ወዴት መካለል እንዳለበት ለመወሰን የማይችል መሆኑን ካመነ የህዝቡን ፍላጎት መጠየቅ ይኖርበታል፡፡እዚህ ላይ የህዝብ ትርጉም ምንድን ነው? (የሚመለከተው ህዝብ ማን ነው?) የሚለውን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ የፌዴራሉ ህገ መንግስት አንቀፅ 48/2/ እንደሚያስግነዝበው ክልሎች በድንበር ውዝግቡ ረገድ መስማማት ካልቻሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድንበር ውዝግቡን (የድንበር የአከላለል ለውጥ ጉዳዩን) የህዝብን አሰፋፈርና ፍላጎት መሰረት በማድረግ ይወሰናል፡፡ ህዝብ ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ነጥብ ከህገ መንግስቱ አንቀፅ 48/2/ አኳያ መመርመር ያስፈልጋል፡፡ እንዲሁም የፌዴራሉ ህገ መንግስት አንቀፅ 48/2/ ከህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ጋር ተጣምሮ ሊመዘን ይገባል፡፡

ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ ምን ማለት እንደሆነ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ትር¹ሜ ሰጥቷል፡፡በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 2/5/ ላይም ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ ምን ማለት እንደሆነ ትር¹ሜ ተሰጥቷል፡፡ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 46/2/ እንደሚደነግገው ክልሎች ከሚዋቀሩባቸው መስፈርቶች አንዱ፤ የሕዝብ ፈቃድ ነው፡፡ የሕዝብ ፈቃድ /ፍላጎት/ ምንድን ነው? የየትኛው ህዝብ ፈቃድ ነው በመስፈርትነት የሚወሰደው? የህዝብ ትርጉም ምንድነው? በአንቀፅ 46/2/ እና በአንቀፅ 39/5/ መካከል የህዝብ ትርጉም ልዩነት አለ ወይ? በብሔር፣ በብሔረሰብ ወይም በህዝብ መካከል የትርጉም  ልዩነት አለ ወይ? የህዝብ ፈቃድና የህዝብ ፍላጎት ይለያያሉ ወይ? ድንጋጌው ህዝብ የሚለውን ቃል የተጠቀመበትን አግባብ ለመረዳት ምናልባት የዚህን ድንጋጌ የእግሊዘኛው ቅጂ አብሮ ማየት ሳያስፈልግ የማይቀር በመሆኑ እንመልከተው፡፡ የዚሁ ድንጋጌ የእንግሊዘኛው ቅጂ – – – the content of the people concerned; በማለት ይጠቅሳል፡፡ እንዲሁም አንቀፅ 48/2/ ደግሞ በተመሳሳይ #የሕዝብ ፍላጎት; በማለት ደንግ¹ል፡፡ የዚሁ እንግሊዘኛ ቅጂ እንዲሁ – – – the wishes of the peoples concerned; በማለት ገልፃል፡፡

በእነዚህ ድንጋጌዎች (በአንቀፅ 46/2/ እንዲሁም አንቀፅ 48/2) ላይ የህዝብ ትርጉም በተለየ ሁነታ አልተደነገገም፡፡ በመሆኑም ትርጉሙን ለማወቅ የህገመንግስቱን አንቀፅ 39/5/ ላይ የተጠቀሰውን የህዝብ ትርጉም መመርመር ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ ይህንን እዚህ ላይ ለጊዜው ገታ አድርገን የህዝብ ፍላጎት የሚለው ሃሳብ ከህገመንግስቱ አንቀፅ 39/3/ እና /5/ ሃሳብ ጋር የሚጣጣም መሆን አለመሆኑን ብንመለከት ይሻላል፡፡

በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ ስር ከተቀመጡት የብሔር አቋም መስፈርቶች ውስጥ ሁለት ተጨባጭ ያልሆኑ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህም ሰዎች የጋራ ወይም የተዛመደ ህልውና አለን ብለው የሚያምኑ መሆን/አለመሆናቸው እና ሰዎች የስነ ልቦና አንድነት ያላቸው መሆን/አለመሆኑ ናቸው፡፡ እነዚህም ባጭሩ የህልውና አንድነት እና የስነ ልቦና አንድነት ልንላቸው እንችላለን፡፡ እነዚህንም ግለሰቦች በሚሰጡት ገለፃ የሚወሰኑ ናቸው፡፡ እነዚህ መስፈርቶች በአንቀፅ 46/2/ እና 48/2/ ጋር ከተጠቀሰው የህዝብ ፈቃድ/ፍላጎት ጋር ያለው ግንኙነት ምንድ ነው?

እዚህ ላይ ወደ ህዝብ ትርጉም ስንመለስ፤ ህዝብ ማለት በአንቀፅ 39/5/ እና በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 2/5/ ላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማህበረሰብ ይመስላል፡፡ ይህ ከሆነ፤ የህዝብ ፈቃድ/ፍላጎት የሚለው የየትኛውን ህዝብ ፈቃድ/ፍላጎት ነው? ይህንንም በምሳሌ ለማስረዳት ያህል የወልቃይት ወረዳን በተመለከተ በትግራይና በአማራ ክልሎች መካከል የድንበር ውዝግብ ቢነሳ የድንበሩን ውዝግብ ለመፍታት ከመስፈርትነት የሚገባው የትግራይ ህዝብ ወይስ የአማራ ህዝብ ፈቃድ/ፍላጎት ነው? ፈቃዱ/ፍላጎቱ የሚለው የትግራይ ህዝብ ከሆነ የውዝግቡ አፈታት ምናልባት ፍትሐዊ ላይሆን ይችላል፡፡ እንዲሁም የአማራ ህዝብ ነው ቢባል እንዲሁ ኢፍትሐዊ ይመስላል፡፡

በሌላ በኩል ህዝብ የሚለው የድንበር ውዝግብ በተነሳበት ቦታ ላይ ብቻ የሚኖሩ ናቸው እንዳይባል የህገመንግስቱ አንቀፅ 39/3/ እና /5/ ከሚደነግገው ጋር አይስማማም፡፡ ከዚህም ባሻገር የእንግሊዘኛው ቅጂ አንቀፅ 48/2/ የሚደነግገው … the wishes of the peoples concerned.; በሚል ነው፡፡ ይህም በአማርኛ ሲተረጎም …በሚመለታቸው ህዝቦች ፍላጎቶች; የሚል ትርጉም ይኖረዋል፡፡ የሚመለከተው ህዝብ የሚለው አገላለፅ በምን አግባብ የሚመለከተው ህዝብ ለማለት ነው? በህገመንግስቱ አንቀፅ 39/2/ ላይ እንደተደነገገው ማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪኩን ና ማንነቱን የመንከባከብና የመጠበቅ መብት አለው፡፡ በሌላ አገላለፅ ማናቸውም ህዝብ ማንነቱን የምያንቀባርቐቑ እስቶችን(መገለጫን)  የመጠበቅ መብት አለው፡፡ በአንቀፅ 39/5/ እንደተገለፀው የማንነት መገለጫ ከሆኑት ጉዳዩች አንዱ የህዝቡ መልክዓ ምድር ነው፡፡ በዚህ ብሄሩ የሰፈረበት መልክዓ ምድር አጠባበቅ ረገድ የድንበር ውዝግብ ከተነሳበት ቦታ ከሚኖሩት የተወሰኑ የህዝቡ ክፍል ፈቃድ/ፍላጎት ባለፈ ባወዛጋቢው ድንበር ላይ ክልል የመሰረተው አጠቃላይ ብሄር ፍላጎት/ፈቃድ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ካልሆነ አንድ ብሔር እንዴት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የብሄሩን  መልክዓ ምድር ጠብቆ በማቆየት ወደ ቀጣዩ የብሔሩ ትውልድ ሊያስተላልፍ ይችላል፡፡ በዚህ አግባብ ካልሆነ በቀር ብሔሩ ታሪክና መክዓ ምድሩን ጠብቆ ሊያቆይ የሚችልበት ሌላ መንገድ የለም፡፡ በመሆኑም ፈቃድ/ፍላጎት መጠየቅ የሚገባው የድንበር ውዝግብ የተነሳበት ቦታ የሰፈረውን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ከዚያ ባለፈ የሚኖረውን የህዝቡ ክፍልን ጨምሮ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ይሁንና ይህ ከመወሰኛው አንዱ መስፈርት እንጂ ብቸኛው መስፈርት አይደለም፡፡

ከዚህም በላይ እዚህ ላይ አንድ ሌላ ነጥብን መመርመሩ ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ ይህንንም በምሳሌ ማስረዳት ይሻላል፡፡ ለምሳሌ በወልቃይት ወረዳ ላይ በትግራይና በአማራ ክልሎች መካከል የድንበር ውዝግብ መካከል ተነሳ እንበል፡፡ ወልቃይት የድንበር ውዝግብ በተነሳበት ሰዓት በትግራይ ክልል ወሰን ውስጥ ተካሎ የሚገኝ እንደሆነ ግልፅ ሲሆን በወልቃይት ወረዳ ሆነ በትግራይ ክልል ውስጥ ከትግራይ ተወላጆች ውጭ የሆኑ የተለያዩ የኢትዮጵያ ብሄሮች ተወላጆች ተበታትነው እንደሚኖሩ ከ1984 እና ከ1999 የህዝብና የቤቶች ቆጠራ ውጤት መግለጫ መረዳት ይቻላል፡፡ በአማራ ክልል ውስጥ ዕውቅና ካገኙ ብሄሮች ውስጥ የወልቃይት ወረዳ ይገባኛል የሚለው ብሄር አማራ ነው ብለን እናስብና በዚህ ዓይነት የድንበር ውዝግብ ላይ ከአማራና ከትግራይ ውጪ የሆኑ ሌሎች የኢትዮጵያ ብሄሮች በድንበር ውዝግብ አፈታት ላይ ፈቃዳቸውን/ፍላጎታቸውን ሊገልፁ ይችላሉ ወይ የሚለውን ጥያቄ መታየት ይኖርበታል፡፡

የድንበር ማስከበር መብት የተረጋገጠው እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብሄር የሰፈረበትን መልክዓ ምድር ጠብቆ እንዲያቆይ ነው፡፡ ይህ ከሆነ፤ እንዴት የድንበር ውዝግብ በተነሳበት ቦታ ሰፍሬአለሁኝ/ይገባኛል በማለት ያልጠየቁ ብሄሮች ፍላጎታቸውን ሊገልፁ ዕድሉ ይሰጣቸዋል? እንደዚህ ፅሑፍ ፀሐፊ እምነት የድንበር ውዝግብ በተነሳበት ቦታ ላይ ሰፍሬአለሁኝ ከሚሉት ብሔሮች ውጪ ያሉ ብሔሮች በጭራሽ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ሊገቡ አይችሉም፡፡ ምክንያቱም እያንዳንዱ ብሔር የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት ያለው በሰፈረበት መልክዓ ምድር በመሆኑ ነው፡፡ የክልሎች የድንበር ውዝግብ ምክንያት የሚሆነው በአወዛጋቢው ድንበር ክልል ውስጥ የሰፈረው ብሔር የኔ ነው፤ የኔ ነው በሚል በመሆኑ በዚህ ውዝግብ ውስጥ ሚና ሊኖራቸው የሚገባው በቦታው ላይ ሰፍረናል የሚሉት ብሔሮች ብቻ ናቸው፡፡

ሦስተኛው ዓይነት መንገድ ደግሞ በክልሎች መካከል በሚደረግ ስምምነት መሰረት የድንበር ውዝግቡን መፍታት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የስምምነቱ አካላት የሚመለከታቸው ክልሎች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ ከሦስቱ የክልል መንግስት አካላት ማን ነው? ስምምነት ሊያደርግ የሚችለው የሚለው መታየት አለበት፡፡ በህገመንግስቱ አንቀፅ 50/2/ መሰረት ክልሎች የህግ አውጪ፣ የህግ አስፈፃሚ እና የዳኝነት አካላት አላቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ማን ከሌላ ክልል ጋር ቁጭ ብሎ ይደራደራል የሚለው ነጥብ ለየክልሎች የተተወ ጉዳይ ይመስላል፡፡

አራተኛው ዓይነት መንገድ ደግሞ በፌዴራሉ ህገመንግስት አንቀፅ 49/4/ ላይ ተመልክቷል፡፡ በጥቅምት 18 ቀን 1987 ዓ.ም በተወካዩች ምክር ቤት በፀደቀው የህገመንግስት ረቂቅ አጭር ማብራሪያ ላይ አዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ተመልክቲል፡፡ እንዲሁም የህገ መንግስቱ ቃለጉባኤ ላይ አዲስ አበባ የኦሮሞ መኖሪያ ናት ተብሎ ተጠቅሷል፡፡ በዚህ አኳኃን ህገመንግስቱ በራሱ አዲስ አበባ የኦሮሞ ህዝብ ወሰን መሆኑን ወስኗል፡፡ ሆኖም የውሳኔው መስፈርት ምን እንደሆነ ምናልባት ግልፅ አይደለም (Obviously it is not stipulated  based on settlement patterns, but rather it seems based on historical homeland)፡፡ እንዲሁም የአዲስ አበባ የድንበር ወሰን የት ድረስ እንደሆነ በምን አግባብ እንደሚወሰንም ሆነ ማን እንደሚወስንም አልተደነገገም፡፡ የህገመንግስቱ አንቀፅ 46/2/ና 48(2) ድንጋጊዎች ስለአዲስ አበባ ከተማ የድንበር ወሰን አከላለል አግባብነት የላችውም፡፡ የህገመንግስቱ ማብራሪያ እንደሚያስገነዝበው የአዲስ አበባ ወሰን ህገመንግስቱ በፀደቀበት የነበራት ወሰን ሲሆን ወሰኑም ወደ ፊት እየሰፋ የሚሄድ በመሆኑና የወሰን መስፋት ጉዳይ በሚኖር ጊዜ ኦሮሚያ በምታቀርበው (በምታጣው) መሬት አግባብ ልክ ልዩ ጥቅሟ ይከበራል፡፡ የሚጠበቀው ልዩ ጥቅም ምን እንደሆነና በምን አግባብ እንደሚጠበቅ በዝርዝር ህግ የሚደነግግ መሆኑን ህገመንግስቱ ደንግጓል፡፡

አምስተኛው ደግሞ የህገመንግስቱ አንቀፅ 46/2/ና 48(2) እንደደነገጉት አንድ ክልል ብዙ ብሔሮች አካቶ በያዘ ጊዜ ክልሉ የሚዋቀሩት በህዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ፤ ማንነት እና ፈቃድ ላይ በመመስረት እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

2.3 የድንበር ውዝግብ መወስኛ መስፈርት

የህገ መንግስቱ አንቀፅ 39/3/ እንደሚያስገነዝበው ማንኛውም ዕውቅና ያገኘ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ በሰፈረበት መልክዓ ምድር ውስጥ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት አለው፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት የብሔሩ መልክዓ ምድር የሚባለው ብሔሩ የሰፈረበት መልክዓ ምድር ነው፡፡ ስለዚህ መስፈር (ሰፈራ)/territorial disputes or claims settlement interms of settlement patterns of the people/ መሰረታዊ የድንበር ወሰን መወሰኛ መስፈርት ነው፡፡

የህገመንግስቱ አንቀፅ 39/5/ አንድ ማህበረሰብ የብሄር ማህበረሰብ አቋም ለማግኘት ሊያሟላቸው ከሚገባቸው መስፈርቶች አንዱ ማህበረሰቡ በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩ; መሆናቸው ነው፡፡ ድንበር ይገባኛል ለማለት መሰረታዊ መስፈርቱ በመልክዓ ምድሩ ውስጥ መኖር (inhabitation) ነው፡፡

የህገመንግስቱ መግቢያ ደግሞ እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች ወይም ህዝቦች…….የየራሳችን መልክዓ ምድር አሰፋፈር የነበረንና ያለን …… በማለት ይገልፃል፡፡ This expression seems referring with hesitative tone to the concept of historical homeland. በዚህም መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር የድንበር አከላለል ለመወሰንም ሆነ የድንበር ውዝግብ ለመፍታት ወሳኙ መስፈርት ነው፡፡

የህገመንግስቱ አንቀፅ 46/2/ ደግሞ ክልሎች የሚዋቀሩት በህዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ ማንነት እና ፈቃድ ላይ በመመስረት እንደሆነ ተደንግ¹ል፡፡ በአንቀፅ 47/1/ መሰረት የተወሰኑ ብሄሮች የየራሳቸውን ክልል የተቋቋመላቸው ሲሆን አንቀፅ 47/2/ ደግሞ የየራሳቸውን ክልል ያልተቋቋመላቸው ብሄሮች የየራሳቸውን ክልል በማናቸውም ጊዜ የማቋቋም መብት እንዳላቸው ደንግ¹ል፡፡ በዚህ አኳኃን ክልሎች በሚቋቋሙበት ጊዜ መዋቀር የሚገባቸው ብሔር ያቋቋመው/የተቋቋመለት ብሄር በሰፈረበት መልክዓ ምድር ነው፡፡ በመሆኑም አንቀፅ 46/2/ ከህገመንግስቱ መግቢያ፣ አንቀፅ 39/3/ እና 39/5/ ተቆራኝቶ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል፡፡ እዚህ ላይ አንድ ብሄር የራሱን ክልል በሚያቋቁምበት/በተቋቋመለት ጊዜ የሚኖረው የክልል አከላለል መስፈርት እና ብዙ ብሔሮች ተጠቃለው በአንድ ክልል ውስጥ በታቀፉበትና በሚታቀፉበት ጊዜ የሚኖረው የክልል አከላለል መስፈርት ይለያያል፡፡ አንድ ብሄር የራሱን ክልል በሚያቋቁምበት/በተቋቋመለት ጊዜ ክልሎ የሚዋቀሩት በህዝብ አሰፋፈር ላይ በመመስረት እንደሆነ ተደንግ¹ል፡፡ ብዙ ብሔሮች ተጠቃለው በአንድ ክልል ውስጥ  በሚታቀፉበት ጊዜ ክልሎ የሚዋቀሩት በህዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ ፤ማንነት እና ፈቃድ ላይ በመመስረት እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

በሌላ በኩል የህገመንግስቱ አንቀፅ 48/2/ ደግሞ የክልሎች ወሰን ለውጥ በሚመለከት ጥያቄ የተነሳ እንደሆነ እና ጉዳዩ በሚመለከታቸው ክልሎች መስማማት ካልተቻለ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የህዝብ አሰፋፈርና ፍላጎት መሰረት በማድረግ ይወስናል ብሎ ጠቅሷል፡፡ ይህ ድንጋጌ በአንቀፅ 46/2/ ድንጋጌ ውስጥ የተጠቀሱትን የቋንቋና የማንነት መስፈርቶች ከድንበር ውዝግብ አፈታት መስፈርትነት አስወግዷቸዋል፡፡ በዚህም የተነሳ በአንቀፅ 46/2/ እና 48/2/ መካከል ግልፅ መጣረስ እንዳለ መገንዘብ የሚቻል ይመስላል፡፡ አንቀፅ 46/2/ የክልሎች ድንበር(ወሰን) የቅድሚያ (የመጀመሪያ) አከላለል መስፈርቶችን የደነገገ ሲሆን አንቀፅ 48/2/ ደግሞ የክልሎች ድንበር ለውጥ አወሳሰን(አደራረግ) መስፈርቶች አደራጅቷል፡፡ በመሆኑም በእነዚህ ጉዳዩች ላይ የተለያዩ መስፈርቶች ያሉ በመሆኑ በኢትዮጵያ የፌዴራል አተገባበር ሂደት ውስጥ የማያቋርጥ ክልሎች የድንበር ውዝግብ እንዲነሳ የሚጋብዝበት ሁኔታ የሚፈጥር ይመስላል፡፡ ስለሆነም አንቀፅ 48/2/ ከአንቀፅ 46/2/፣ 39/3/፣ 39/5/፣ ከህገመንግስቱ መግቢያና ከአጠቃላይ የህገመንግስቱ ይዘት፣ መንፈስና ዓላማዎች አኳያ አገናዝቦ ገቢራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የድንበር ውዝግብ በብሔር መልክዓ ምድር አሰፋፈር መሰረት ሊወሰን ይገባዋል፡፡ ይኸውም አሰራር ከህገመንግስቱ መግቢያ፣ ከአንቀፅ 39/3/፣ 39/5/፣ 46/2/ እና ከህገመንግስቱ መርሆዎች ጋር በሚገባ የተናበበና የተጣጣመ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡

በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 28/1/ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የህዝብን አሰፋፈር በማጥናት አከባቢው ወደ የትኛው ክልል መካለል እንዳለበት ለመወሰን ሚያስችል በቂ መረጃ እንዳለው ካመነ በዚያው መሰረት ይወሰናል፡፡የአዋጁ አንቀፅ 28/2/ እንደሚያስገነዝበው የፌዴሬሽን ምክር ቤት የህዝቡን አሰፋፈር በማጥናት አከራካሪው አከባቢ ወዴት መካለል እንዳለበት ለመወሰን የማይችል መሆኑን ካመነ የህዝቡን ፍላጎት መጠየቅ ይኖርበታል፡፡ የህዝቡን ፍላጎት ለመጠየቅ ህዝበ ውሳኔ ማድርግ ያስፈልጋል፡፡እነዘህ ድንጋጌዎች የህዝብን አሰፋፈር እና የህዝቡ ፍላጎትንን/የክልሎች ድንበር ለውጥ አወሳሰን (አደራረግ) መስፈርቶችን ማራጮች (alternatives) ድርገዋቸዋል፡፡በዚህም የተነሳ በአዋጅ ቁጥር 251/1993 አንቀፅ 28/1/ና 28/2/ እና የህገመንግስቱ አንቀፅ 48/2/ መካከል ግልፅ መጣረስ እንዳለ መገንዘብ የሚቻል ይመስላል፡፡ የሚጋጨው ግን ብዙ ብሔሮች ተጠቃለው በአንድ ክልል ውስጥ  በሚታቀፉበት ጊዜ መስፈርቶቹ ማራጮች በሆኑ ግዜ ነው፡፡

 በአጠቃላይ የድንበር ውዝግብ የሚወሰነው በሕዝብ አሰፋፈር መስፈርት ነው፡፡ ይህም ማለት በአወዛጋቢው ድንበር ላይ የሚኖረው የትኛው/የቱ ብሔር ነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ ነው ጉዳዩን የሚወስነው፡፡ በመሆኑም በአወዛጋቢው ድንበር ላይ የሚኖረው ብሄር የቱ እንደሆነ በምን መንገድ መወሰን ይገባል? መወሰኛ መንገዶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህም፡-1ኛ/ በገለልተኛ አካል አስተያየት በድንበሩ የሰፈረውን ብሄር መወሰን ወይም/እና 2ኛ/ የሚመለከተው ህዝብ የየትኛው ብሔር አባል እንደሆነ ህዝበ ውሳኔ እንዲገልፅ በማድረግ ናቸው፡፡

3.ታሪክ ቀመስ ዳሰሳ ባጭሩ

ይህ ክፍል የትግራይ ህዝብና የወገራ ግዛት(ወልቃይትና አከባቢቹ) ታሪካዊ ግንኙነቶችን በተመለከተ ለመቃኘት ታሪክ ቀመስ ማስታወሻ ይዟል፡፡ በሌላ አገላለፅ ስለ ትግራይ ህዝብ መልክዓ ምድራዊ አሰፋፈር ታሪክ ዳሰሳ (ከታሪካዊ ሰነዶች) ባጭሩ በዚህ ክፍል ስር ተደርጓል፡፡

Harold G.Marcus “A History of Ethiopia” በሚለው መፅሐፍ ላይ እንዳረጋገጠዉ አክሱማዉያን ከተከዘ በስተደቡብ የሚገኘዉን የአገዉ ምድርን በማስገበርና የሰሜን ተራሮችን በመቆጣጠር ወታደራዊ መስፋፋት አድርገዉ ነበር፡፡ የአክሱም መንግስታዊ ሀይል የደቡብ ትግራይ አካባቢን በማጠቃለል ዋግና ላስታን በመያዝ እስከ ሰሜን ወሎና አገዉ ምድር ድረስ (በጌምድርን ጨምሮ) እሰከ 10ኛ ክ/ዘመን መጨረሻ ለመስፋፋት ችሏል፡፡

Serqew Habte selassie በፅሑፉ እንደጠቀሰው የአክሱም ግዛቶች መሃል ሂያምር፣ ራይዳን፣ ሳብና ሐለን በደቡብ ዓረቢያ የሚገኙ ሲሆን ፁያም ጋምቤላ እንደሆነ ቤጋ የሚለው ደግሞ ቤጃ እንደሆነና ጠቅላላ ግዛቱ ምዕራባዊ ኤርትራ አካቶ እስከ ምስራቅ ሱዳን ይደርስ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን የአክሱም ግዛት ደጀግ ሰፈ እንደሆነ በአራተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነግሶ የነበረው ንጉስ ኢዛና የተወው የድንጋይ ላይ ፅሑፍ በግልፅ ያመለክታል፡፡ ንጉስ ኢዛና የኑቢያን እና የቸንተን ግዛቶች ጭምር በቁጥጥር ስር በማድረግ ያስተዳድር እንደነበር የተለያዩ የታሪክ መዛግብቶች በሚገባ መስክረዋል፡፡ ኑብያ ከአባትራ ወንዝ በስተምስራቅ ያለውን የሱዳን ሰሜን ምስራቅ ክፍል አካቶ የሚይዝ ሲሆን የቸንት ግዛት ደግሞ እስከ ከቀይባህር በስተደቡብ ያለውን ግዛት አተቃልሎ እንደሚይዝ የተለያዩ የታሪክ መዛግብት ዘግበዋል፡፡

ማኑኤል ባራዳ የተባለው ፖርቹጋላዊ ሚሲዩን በ17ኛው ክፍለ ዘመን የትግራይ ታሪካዊና ጂኦግራፊያዊ ዘገባ በሚል ርዕስ በ1634 እ.ኤ.አ በፃፈው ፅሑፍ ላይ የትግራይ አገር አዋሳኞች በስተደቡብ በኩል አልውሃ (አላማጣና ወልዲያ) ፣ በስተሰሜን ሐማሴን; በስተምስራቅ ደግሞ ጋማከል/አማከል( የአፋር በርሃ); በስተምዕራብም ሊማሊሞ(ድብ ባህር); እንደሆነ በጣም ግልፅ በሆነ ሁኔታ በካርታ ንድፍ አስቀምጧል፡፡ ይህ ሚሲዩናዊ ይህንን ፅሑፍ በፃፈበት ጊዜ የኢትዩጵያ ንጉስ ፋሲለደስ ነበር፡፡ ፅሑፉን ከመፃፉ በፊት በኢትዩጵያ ውስጥ ረመና በሚባል ቦታ በሚሲዮናዊነት ሲኖር ከቆየ በኃላ ሚሲዮናዊያን በሱሲንዩስ እና በፋሲለደስ እንዲባረሩ ሲደረግ እሱም ወደ ኤደን (የመን) ሄደና ይህን ፅሑፍ በየመን ሆኖ ፃፈ፡፡

ከዚህ ባሻገር በ17ኛው ክፍለ ዘመን ደጃዝማች ገላውዲዩስ የተባለው የሽሬ ገዥ ወልቃይትን ጠቅልሎ ያስተዳድር የነበረ ስለመሆኑ በተለያዩ የታሪክ መዛግብት ላይ ተመስክሯል፡፡ ደጃዝማች ገላውዲዩስ ወልቃይትን ብቻ ሳይሆን ቆላውን አከባቢ እና በታቾቹ ድረስ ያስተዳድር እንደነበር የታሪክ ሰነዶች ይመሰክራሉ፡፡

በ1930ዎቹ መጀመሪያ ደግሞ ራስ ጉግሳ ወሌ በጌምድርን ያስገብር ነበር፡፡ራስ ጉግሳ ወሌ በጌምድርን ሲያስገብሩ በነበረበት ጊዜ ራስ ጉግሳና ራስ ተፈራ (በኃላም ንጉስ ሃይለስላሴ) ግጭት ውስጥ ይገባሉ በዚህም ግጭት ራስ ጉግሳ ወሌ ተሸነፈ፡፡ ከዚህ በኃላ ጣሊያን ተሻግሮ ኢትዮጵያን ለቆ ከሄደ በኃላ አፄ ኃይለስላሴ ወልቃይትና አከባቢውን በጌምድር እና ሰሜንን ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ቀላቅለው የሸዋ አማሮችን እያፈራረቁ በግዛቱ ላይ ለ33 ዓመታት ሾመውበታል፡፡

በ1930ዎቹ ላይ FREDRICK SIMOONS አከባቢውን ለሶስት አመት ጎብኝቶና አጥንቶ “NorthWest Ethiopia: Peoples And Economy “በሚለው መፅሐፍ ላይ   እንደመሰከረው የወልቃይት ወረዳ ትግራዊያን የሰፈሩበት መልክዓ ምድር እንደሆነ ገልፃል፡፡ በተመሳሳይ DONALD N. LEVINEን ”The Greater Ethiopia፡ The Evolution Of A Multiethnic Society” በሚለው መፅሐፍ ላይ እንዳረጋገጠው ደብረታቦር የክፍለሃገር መገበያያ ቦታ መሆኑን ጠቅሶ በዚህ የገበያ ቦታ ላይ ገበያተኞች ከቅማንት ወረዳ ከሆነው ከጭልጋ (people brought ginger from chiliga, a kimant district) በእግር ስድስት ቀን ተጉዘው ጅንጅብል እንደሚያቀርቡ፣ ገበያተኞች ከአማራው ወረዳ ከጋይንት (wool saddle blankets from gaint, an amhara district) በእግር ሶስት ቀን ተጉዘው የሱፍ ብርድ ልብስ እንደሚያቀርቡ፣ ገበያተኞች ከትግራዊያን ወረዳ ወልቃይት (cotton from the Tigrean district of wolqait) 11 ቀን በእግር ተጉዘው ጥጥ ደብረታቦር እንደሚያቀርቡ መስክሯል፡፡ ፍሬዴሪክ ሲሞንና ዶናርድ ሌቪን እንደመሰከሩት ወልቃይት የትግራዊያን ወረዳ ነው (ትግራዊያን የሰፈሩበት መልክዓምድር) መሆኑን መስክረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ኤልቤርቶ ሰባኪ እ.ኤ.አ.1985 “Ethiopia Under Mussoloni: Fascism and The Colonial Experience” በሚል በፃፈው መፅሐፍ ላይ እንዲህ ብሏል ’… ሌሶና የአማራ ጠቅላይ ግዛት አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ ግዛቶች ብቻ እንዲይዝ ቢከራከርም ፀለምት በአብዛኛው ትግርኛ ተናጋሪ አከባቢ ቢሆንም የጠቅላይ ግዛቱን ወሰን የተከዜን ወንዝ በመከተል ለመከለል ሲባል ወደ አማራ ተከልሏል፡፡ ሌሎች እንደ ወልቃይትዋልድባ፣ ፀገዴ፣ ሰሜን፣ ወገራ እና በለሳን የመሳሰሉ ግዛቶች ከአማራ ይልቅ በትግርኛ ተናጋሪዎች የተያዙ (ትግርኛ ተናጋሪዎች የሰፈሩበት) እና ከኢጣሊያ ወረራ በፊት ከሰቲት ወንዝ በስተደቡብ የሚገኙት እነዚህ አከባቢዎች (ግዛቶች) የኢኮኖሚ ግንኙነታቸው ከጎንደር ይልቅ ከአስመራ ጋር እንደሆነ በሚገባ አጥንቶ መስክሯል፡፡ ኢጣልያ ኢትዮጲያን በምታስተዳድርበት ጊዜ በስድስት ጠቅላይ ግዛቶች ከፋፍሎ የነበረ ሲሆን ክፍፍሉም በድንበሩ ላይ የሰፈረውን ብሄር ማንነት መስፈርት በማድረግ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር ኤልቤርቶ ሰባኪ በተጨማሪ እንዳረጋገጠዉ የእቴጌ ጣይቱ ወገን የሆኑት ደጃዝማች አያሌዉ ብሩ ለንግስቱ ለነበራቸዉ ታማኝነትና ለሰጡት ድጋፍ ማካካሻ እንዲሆናቸዉ ወልቃይት፣ጸገዴ፣ወገራና የሰሜን የተወሰኑ ክፍለ ግዛት ተሰጥቷቸዋል፡፡

ራስ ሚካኤል ሱሑል በአፄ ኢያሱ ጊዜ ሰሜን ግዛትን ጨምሮ መላ ትግራይ ትግርኚ (ኤርትራን ጨምሮ) እስከ ቀይ ባህር ምፅዋ ድረስ ለአርባ ዓመት  ሲገዙ ነበር፡፡ በኃላም በአፄ ኢዩአስ ስር ከነሙሉ ወታደራቸው መቀመጫቸውን ጎንደር አድርገው ኢትዩጵያን በእደራሴነት ከአስር ዓመት በላይ ገዝተዋል፡፡

ደጃዝማች ወ/ስላሴ እ.ኤ.አ. ከ1809 ድምሮ ትግራይን የወገራን ግዛት ጨምሮ መርተዋል፡፡የሰሜን ግዛት የወገራን ግዛትን የማያጠቃልል ሲሆን የወገራ ግዛት ደግሞ ወልቃትን፤ጸገዴና ጸለምትን ያጠቃልላል፡፡በ1809 አካባቢ ወ/ስላሴ በወገራ ግዛቱ በኩል አጎራባች ከሆነዉ የሰሜን ግዛት መሳፍንቶች ደጃዝማች ገብሩና ራስ ሀይለማርያም ጋር ግንኙነቱን በማጠናከር ሲገዛ ነበር፡፡ዶናልድ በመጽሃፉ ላይ በካርታ ጥምር እንደጠቆመው የበጌምድር ግዛት፤ የደምቢያን፤ የሰሜንንና የወገራን (የወልቃትንና ሌሎች አካባቢዎች) ግዛቶች አካቶ አይዝም፡፡ ይህንኑ ለመመገንዘብ ቀጥሎ ያለውን በዶናልድ በመጽሃፉ ላይ የተካተተውን  ካርታ ይመልከቱ፡፡

Map – Amhara homeland and sphere of influence about 1520

ዶናልድ በመጽሃፉ ላይ እንደጠቆመው የራያ ኦሮሞዎች ከአርብቶ አደር ባህላቸውን በአብዛኛው ጠብቀው ቢቆዩም ከትግራውያን ጎረባቶቻችውና ተፈናቃዮቻቸው የትግርኛ ቋንቋን የወርሰዋል፡፡ የኦሮሞ ሃገርና በ17ኛው ክፍለ ዘመን በመስፋፋት የያዟቸውን አከባቢዎች በዶናልድ መጽሃፉ ላይ ከተካተተው ቀጥሎ ካለው ካርታ ይመልከቱ፡፡

Map – Oromo homeland and area of conquests about 1700

Harold G.Marcus አጥንቶ እንዳረጋገጠዉ ወ/ስላሴ አዘቦ(ራያ) ግዛትን ብቻቸዉን በማስመለስ እና ወደ ትግራይ መተላለፊያ የነበረዉን ላስታን በመያዝ አቋሙን ማሳየቱን ገልጧል፡፡ በመቀጠልም ወ/ስላሴ ወደ ጠረፍ ዘምቶ የሙስሊሙን ንግድ ተቆጣጥሮ ማስገበር ቻለ፡፡ በዘመነ መሳፍንት የትግራይ ገዢዎች እንደሌሎቹ ትልልቅ ክፍለ ሃገሮች ሁሉ ራስ ገዝ የሆኑ ግዛቶች ነበሩዋቸው፡፡ ከእነዚህ የትግራይ ግዛቶች ውስጥ ብዙዎቹ ልዩ ልዩ ተወዳዳሪ አውራጃዎች ተደማምረው ነፃ ራስ ገዝ ጠቅላይ ግዛት የሆኑት ደጃዝማች ስባጋድስ ስልጣን ከያዙ በኃላ ነው፡፡

ደጃዝማች ስባጋድስ ትግራይንና ኤርትራን ከነቀይባህሩ ( እስከ ምጽዋ አካባቢ አለዉሃ ምላሽ) ጋር በአንድ ላይ በመስፍንነት ከ1808-1823 ድረስ ገዝተዋል፡፡ የደጃዝማች ስባጋድስ  የእነዚህ  ግዛታቸዉ ድንበር ወሰን የሰሜኑ ባላባት ከሚያስተዳድረዉ ሰሜን ግዛት በስተስሜን በኩል የሚገኙትን ወገራን ግዛት( የወልቃይትና አካባቢዎችን) አጠቃሎ የያዘ ነዉ፡፡ የየጁን መዳከምን የተመለከተዉ ሱባጋድስ የደጃዝማች ወ/ስላሴን አላማ በመከተል ሰሜኑን፣ በጌምድርን እና አካባቢዉን ከትግራይ ጋር በመቀላቀል ጎንደር ላይ መንግስቱን ለመመስረት ተንቀሳቅሷል፡፡ የላስታው ገዥ ማርዬ በጌምድርን፣ የጁንና ወሎን በማሰገበር ደጃዝማች ስባጋድስን ለመውረር ተነሳ፡፡ በ1831 ዓ.ም ራስ ማርዬ የጁንና ወሎን ምርኮኞቹን አስከትሎ ከጎንደር በስተሰሜን ወደምትገኘዉ ደብረ ባይ ስባጋድስ ወደሚገኙበት ቦታ ዘምተዉ ሲዋጉ የሞቱ ሲሆን ስባጋድስ ከውጊያው በሃላ ሞት ተፋርዶባቸው በሞት ተቀጥተዋል፡፡

የትግራዩ መስፍን ደጃዝማች ስባጋድስ ከሞቱ በኃላ በእርሳቸዉ ቦታ ደጃዝማች ዉቤ ሀይለማርያም ደጃዝማች ስባጋድስን ተክተዉ ትግራይ ትግሪኝ ሰሜንን ጨምረዉ ከ1823-1845 ድረስ ለሀያ ሶስት አመታት ገዝተዋል፡፡ Harold G.Marcus እንዲሁ እንዳረጋገጠዉ ራስ ዉቤ ሀይለማርያም ትግራይን ወገራንና ሰሜንን ጨምሮ በአንድነት በማስተዳደር የኦሮሞን ሀይል ለማስቆም ችለዋል፡፡ ደጃዝማች ዉቤ ሀይለማርያም ደጃዝማች ስባጋድስ ከመሞታቻዉ በፊት ሰሜንን ሲገዙ የቆዩና ከደጃዝማች ስባጋድስ ጋር በጋብቻ የተሳሰሩ ነበሩ፡፡

አገዉ ንጉሴ በመባል ይጠራ የነበረዉ ወልደሚካኤል በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት ትግራይንና ቤጌምድርን ጠቅልሎ ይገዛ እንደነበር እኝህ ጸሐፊ መስክረዋል፡፡ ወ/ሚካኤል የደጃዝማች ዉቤ ሀ/ማርያም የእህት ልጅ ሲሆን የቴዎድሮስን አገዛዝን ባለመቀበል ታግሏል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባዉ ነገር እስከ እ.ኤ.አ 1943 ድረስ በጌምድር በሚል ስያሜ የሚጠራዉ ግዛት የሰሜን፣የደንቢያ፣የወገራን(የወልቃትንና ሌሎች አካባቢዎች) ግዛቶች አጠቃሎ አያዉቅም፡፡ የሰሜን ግዛት በሚል ስያሜ የሚጠራዉ አካባቢ የወገራን(የወልቃትንና ሌሎች አካባቢዎች) ግዛት አጠቃሎ የማይዝ መሆኑን ብርሃኑ አስርስ ማን ይናገር የነበረ…የታህሳሱ ግርግር እና መዘዙ በሚለው መፅሐፍ ላይ  ገልጧል፡፡  የሰሜንና የወገራ (ወልቃይትና ሌሎች  አካባቢዎች) ግዛቶች ከበጌምድር ግዛት ጋር ለመጀመሪያ ግዜ በታሪክ የተዋሀዱት እ.ኤ.አ በ1943 ነዉ፡፡

ወ/ሚካኤል ትግራይን በጌምድርን ጠቅልሎ ይገዛ ነበር ሲባል የትግራይን እና የበጌምድርን አዋሳኝ ድምበር ከ1943 በፊት በጌምድር ተብሎ የሚጠራዉ ግዛት የስሜን ግዛት ሰሜናዊ ጫፍ መሆኑን ያሳያል፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የበጌምድር ግዛት የዳሞትን፤የደምቢያን፤ የሰሜንንና የወገራን(የወልቃትንና ሌሎች አካባቢዎች) ግዛቶች እ.ኤ.አ እስከ 1943 ድረስ አካቶ የማይዝ መሆኑን ያሳያል፡፡ በ1868 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ሲሞቱ የትግራዊያን የንግስ ሐረግን ለማስመለስ ቀድሞ ለመውጣት ቻሉ፡፡ ለሺ ዓመታት ከተቋረጠ በኃላ ዙፋኑን ወደ ትግራይ በ1871 ዓ.ም የመለሱት ዬሐንስ 4ኛ ኢትዮጲያን ፊደራላዊ በሆነ መልኩ በመልካም ሁኔታ ማስተዳደራቸው እንከን በሌለው ሁኔታ የተመሰከረላቸው ነበሩ፡፡

አጼ ፋሲል ለመናገሻነት የመረጡት ቦታ ቀድሞም ጎንደር ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ ጎንደር የሚለዉ ስያሜ አመጣጥ እንዴት እንደሆነ የጎንደር ከተማ መዘጋጃ ቤት ጋዜጣ  በ1966 አ.ም  ‹‹ትዕይንተ ጎንደር ዜና ›› ጋዜጣ ላይ ወይንአ ሰይንአ የተባሉት ወንድማማቾች ከብዙ አመታት በፊት ከእንድርታ አዉርጃ ኩሐ ተነስተዉ በሰሜን በኩል አቋርጠዉ በአንገረብና በቀሃ ወንዝ የሚገኘዉን ቦታ ይዘዉ ከሰፈሩበት በኃላና አገሩን እያቀኑ ከተባዙ በኃላ ወንድማማቾቹ በድንበር ገፈኸን በመባባል በተጣሉበት ጊዜ ሽማግሌ ከሁለቱ ወንድማማቾች በእድሜ አነስተኛዉን የሆነዉን አይቶ አንተስ ብሆን ምንአለ ‹‹ በሱ ጎን እደር፣ አሁንም ቢሆን አሱ ጎን እደር›› ብሎ በመወሰኑ የተነሳ ቦታዉ ጎንደር ተብሎ ይጠራ እንደነበር ገልጧል፡፡ የሁለቱ ወንድማማቾች ከትግራይ መጥቶ ባዶ ቦታ ላይ እንደሰፈሩና ጎንደር የሚለዉ ስያሜ  በነዚሁ ወንድማማቾች ምክንያት እንደወጣ በ‹‹ትይንተ ጎንደር ዜና ›› ጋዜጣ ላይ ተመስክሯል፡፡ የአጼ ፋሲል አባት የሆነዉ አጼ ሱስኒዮስ ዋና ከተማቸዉ ደንቀዝ የነበረ ሲሆን ልጃቸዉም እስከ 1627 ድረስ መቀመጫቸዉን ደንቀዝ አድርገዉ ነበር፡፡

አጼ ዩሐንስ 4ኛ የኢትየጲያ ንጉሰ ነገስት ሆነዉ ኢትዮጲያን በሚያስተዳድሩበት ጊዜ ልጃቸዉን ራስ አራአያ ስላሴን የጎንደር ገዥ አድርገዉ ሾመዋቸዉ ነበር፡፡ ራስ አራአያ ስላሴ በኃላም የወሎ ገዥ ሆነዉ አስተዳድረዋል፡፡አጼ ዩሐንስ 4ኛ ኢትዮጲያን በሚያስተዳድሩበት ጊዜ ታላቁ ቤተ መንግስትን በመቀሌ ከተማ ቢያሰሩም አብዛኛዉን ጊዜ መቀመጫቸዉ ሐሸንጌ፣ደሴ እና በተለይም ደብረ ታቦር ነበር፡፡ ራስ ስዩም ኢጣሊያ ኢትዮጲያን በምታስተዳድርበት ጊዜ የኢትዮጲያ ሰሜናዊ መስፍን ተብለዉ ላስታን፣ ወግን፣ የጁን፣ ወልቃይትንና ጸገዴን በግዛታቸዉ ስር አጠቃለዉ እንደነበር የታሪክ ሰነዶች ይጠቁማሉ፡፡

Augusto B.Wild ከአድዋ ድል 12 አመት በፈት ትግራይን እንዲሁም የአድዋ ድልን ተከትሎ ትግራይን፤በጌምድር፤የጁና ሸዋን ጎብኝቶ Modern Abyssinia በሚል በጻፋው መጽሃፍ ላይ የሰሜኑ ባላባት ከሚያስተዳድረዉ ሰሜን ግዛት በስተስሜን በኩል የሚገኙትን የወልቃይት፤ጸገዴና አካባቢዎቹ ትግራዊያን እንደሰፈሩበት እና የትግራይ አካል እንደሆኑ አመልክቷል፡፡

በ1984 አ.ም በተደረገዉ ህዝብና ቤቶች ቆጠራ በወልቃይት፣በጸለምት፣በቃፍታ ሁመራ እና በጸገዴ ወረዳዎች ዉስጥ የብሔሮች ስብጥር ምን እንደሚመስል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም መስረት በጸለምት ወረዳ 87,012 የሚሆኑ ትግራዊያን እንደሰፈሩበት እንዲሁም 10,382 አማሮች እንደሰፈሩበት አረጋግጧል፡፡ በወልቃይት ወረዳ ዉስጥ ደግሞ 87,099 ትግራዊያን እንደሰፈሩበት እንዲሁም 2,734 አማሮች እንደሰፈሩበት አመልክቷል፡፡ በቃፍታ ሁመራ ወረዳ ደግሞ 41,999 ትግራዊያን እና 3,800 አማሮች እንደሚኖሩበት በቆጠራዉ ዉጤት ላይ መስክሯል፡፡ በ1999 አ.ም በተደረገዉ ህዝብና ቤቶች ቆጠራ ላይም ውጤቱ ያው ነው፡፡

ከዚህም በላይ፤ በነዚህ አካባቢ የሚገኙ ቦታዎችና ተራራዎች በአብዛኛዉ ስያሜያቸዉ የትግርኛ ቋንቋ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ቃፍታ ሑመራ፤ጸለምት፤ማይካድራ፤ቃብትያ ሶላ፤ አዲሕድረ ወዘተ ስያሜያቸዉ የትግርኛ ቋንቋ ነዉ፡፡ እንዲሁም በእነዚህ አካባቢ የሚገኙ ሰዎች የሚግባቡበት መደበኛ ቋንቋ ትግርኛ እንደሆነ ክፍሉ ታደስ ያ ትውልድ በሚለው መጽሃፉ ቅጽ ሶስት ላይ መስክሯል፡፡

የደርግ መንግስት Class Struggle and The Problem In Eritrea በሚል 1971 አ.ም ባሳተመዉ መጽሃፍ ላይ የሚከተለዉን በሰሜን ኢትዮጲያ የሚገኙትን ብሔረሰቦች ስርጭት የሚያሳየዉን ካርታ አካትቷል፡፡ በዚህ ካርታ ላይም እንደምናየዉ ከተከዘ በስተደቡብ የሚገኙት የወልቃይት፣የጸገዴ፣ጸለምት፣ሁመራ እና ሌሎች አካባቢዎች የትግራይ ብሔረሰብ የሰፈረባቸዉ መልክአምድሮች መሆናቸዉን መስክሯል፡፡

Map – Nationalities in northern Ethiopia in 1970s

4. መደምደምያ

አማሮችና ትግራዊያን በግዛት ፍላጎት ሲፎካከሩ የቆዩ መሆኑን የታሪክ ሰነዶች ዘግበዋል፡፡ የእነኚህ የክፍለ ሃገር ድንበሮች በዚህ የተነሳ ከትውልድ ትውልድ በጣም መለዋወጣቸው ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ የአውራጃ ወይም የወረዳ ልዩነት፤ ለምሳሌ በሸዋ በመንዝና በይፋት መካከል፤ በትግራይ በሽሬ እና በአድዋ መካከል ያለው ልዩነት በክፍለ ሃገር መካከል ከሚገኙት ልዩነቶች ይልቅ በጣም ጎልተው ይታያሉ፡፡ እዚህ ላይ ለመጥቀስ ያህል አማሮች በአገራቸው የመላው አማራ ማህበረሰብ ነን ብለው አባልነታቸውን ከቶ አጥብቀው አያውቁም፡፡ ማንነታቸውን ለመግለፅ በክፍለ ሃገር ደረጃ ጎጃሞች፣ ሸዋዎች በሚል ነው፡፡ በተቃራኒው በትግራይ ህዝብ መካከል የተለየ ቅርብ ግንኙነት ነበርም፤ አለም፡፡ ምንም እንኳን የትግራይ ህዝብ ለምዕተ ዓመታት በአማሮች ነገስታት እንደራሴዎች ስር ሲገዛ ቢኖርም ከአማሮችም ጋር የመፎካከር ባህል ቢኖርም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ማህበረሰብ ዓላማ ጋር አንድ ዓይነት ያላቋረጠ ታማኝነት ጠብቆ ኖሮአል፡፡የትግራይ ህዝብ ለምዕተ ዓመታት በአማሮች ነገስታት እንደራሴዎች ስር ሲገዛ ቢኖርም በዘመኑ ከነበራቸው ችግርና በአከባቢያቸው ጉዳይ ተወጥረው የቀድሞ አባቶቻቸው በአዋሰኗቸው ክፍለሃገራት እየኖሩ አብዛኞቹ ከነበሩበት ሳይነቃነቁ ቆይተዋል፡፡

የትግራይ ህዝብ  የሰፈረበት መልክአምድሮችየትግራይ ጠቅላይ ግዛት(የትግራይ ክፍለ ሃገር) ግዛት ወስን የተለያዩ ናቸው፡፡ በሃይለስላስ ዘመን የትግራይ ጠቅላይ ግዛት( በሃላም በደርግ ዘመን የትግራይ  ክፍለ ሃገር) ግዛት ወስን የተካለለው በድንበሩ ላይ የሰፈረውን ብሄር ማንነት(ቋንቋ)ን መስፈርት በማድረግ ይደለም፡፡የትግራይ ጠቅላይ ግዛት(የትግራይ ክፍለ ሃገር) ግዛት ወስን ተከዘ ነው ማለት የትግራይ ህዝብ የሰፈረው ከተከዘ ወንዝ በስተስሜን  በሚገኙት አካባቢዎች ብቻ ነው ማለት አይደለም፡፡ምክንያቱም ጠቅላይ ግዛት(የክፍለ ሃገር) ግዛት ወስን/መልክአምድርና የትግራይ ህዝብ መልክአምድር ይለያያሉ፡፡ በአሁኑ ህገመንግስት ደግሞ የድንበር አከላለል በአጠቃላይ የሚወሰነው በሕዝብ/በሄሩ አሰፋፈር መስፈርት ነው፡፡ ይህም ማለት በድንበር ላይ የሚኖረው የትኛው/የቱ ብሔር(ሕዝብ) ነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ ነው በሕዝብ/በሄሩ አሰፋፈር የሚወስነው፡፡በመሆኑም የትግራይ ከልል ወስን ተከዘ ነው የሚለው ክርከር መስረት የለውም፡፡

**********

Guest Author

Guest Author

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago