የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙልጌታ፣ የካቲት 18/2008 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ “የኢትዮጲያ መንግስት በታገቱት 80 ኢትዮጲያዊያን ምክንያት በኤርትራ ላይ ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ” ተናግረዋል። መግለጫውን ተከትሎ ከጋዜጠኞች፤ ታጋቾቹ ስለተያዙበት ሁኔታ፣ ማንነት እና መንግስት ሊወስደው ስላሰበው አፀፋዊ እርምጃ ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ ግን በጣም የሚገርም ነው፦”ከዚህ በላይ ምንም ዝርዝር ማብራሪያ ልሰጥ አልችልም”።
በእርግጥ ቃለ አቀባዩ ስለታጋቾቹ ማንነት፣ ስለታገቱበት ሁኔታ ዝርዝር ማብራሪያ መስጠት አይችሉ ይሆናል። ነገር ግን፣ 80 ሰዎች በአንድ ሽፍታ መንግስትና ጋሻ-ጃግሬዎቹ ታፍነው ተወሰዱና 90 ሚ.ህዝብ ለምን ወደ ጦርነት እንደሚገባ ዝርዝር ማብራሪያ እንሻለን። መንግስት በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ መስጠት እንደማይችል ገልጿል። ታሪክ ግን በዚህ ዙሪያ ሰፊና ዝርዝር ማብራሪያ ይሰጣል። ስለዚህ፣ ከመቶ አመት በፊት በተመሣሣይ ችግር ምክንያት የተካሄደን ጦርነት ዋቢ በማድረግ በጉዳዩ ዙሪያ “ዝርዝር ማብራሪያ” ለመስጠት እንሞክራለን።
ከመቶ አመት በፊት፣ ሰኔ 28/1914 (እ.አ.አ) የተጀመረው የአንደኛው ዓለም ጦርነት (WWI) አሁን በኢትዮጲያና በኤርትራ መካከል ስላለው ሁኔታ ጥሩ ማሳያ ነው። በተጠቀሰው ዕለት የኦስትሪያ-ሃንጋሪ አልጋ-ወራሽ የነበረው “Franze Ferdinand” እና ባለቤቱ በሰርቢያ አሸባሪዎች በመገደሉ ምክንያት ሁለቱ ሀገራት ወደ ጦርነት ገቡ። ወዲያው ሩሲያና ፈረንሳይ ከሰርቢያ ጎን፣ ጀርመን ደግሞ ከኦስትሪያ-ሃንጋሪን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገቡ። እንዲህ…እንዲህ እያለ፣ የአንድ አሸባሪ ቡድን ጥቃት ከ15 የሚበልጡ ሀገራት የተሳተፉበት ጦርነት ለመሆን በቃ። በሁለት ሰዎች ሞት የተጀመረው ጦርነት ለ15 ሚ. በላይ ሰዎች ሞት፣ ለ20 ሚ. ሰዎች መቁሰል መነሻ ምክንያት ሆነ። ያን ያህል አሰቃቂ ጉዳት ካስከተለ በኋላ እንኳን የታሪክ ተመራማሪዎች “የ1ኛ ዓለም ጦርነት ለምን ተጀመረ?” ብለው ይጠይቃሉ።
አሁን በኢትዮጲያ እና ኤርትራ መካከል በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና በጦር-መሣሪያ የበላይነት ለመያዝ የሚደረገው ፉክክር ልክ የ1ኛው የዓለም ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ሁኔታ ጋር ተመሣሣይ ነው። በእንደዚህ ያለ ሁኔታ ውስጥ፣ የ2 ሰዎች ሞት የዓለም ሀገራት ወደ ጦርነት እንዳስገባ ሁሉ፣ የ80 ሰዎች ታግቶ መወሰድ ሁለቱን ሀገራት ወደ ጦርነት ሊያስገባ እንደሚችል እርግጥ ነው። ሆኖም ግን፣ በአንደኛው ዓለም ጦርነት ተሳታፊ የነበሩ ሀገራት ከዚያን ዓይነት አሰቃቂ ጦርነት መቶ አመት ወደፊት ርቀው ሄደዋል። እኛ ግን እነሱ ከመቶ አመት በፊት በነበሩበት ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው።
ሀገራት መተባበር ካልቻሉ መተማመን ይሳናቸዋል። ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በኢትዮጲያ እና ኤርትራ መካከል ጦርነት እንጂ ትብብር አልነበረም። ሁለቱ መንግስታት ችግሮቻቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ተነጋግረው በመፍታት ትብብር መፍጠር ስላልቻሉ በሁለቱ ሀገራት መካከል መተማመን ሊኖር አልቻለም። በሁለቱ ሀገራት መካከል ሌላ ምንም አሳማኝ ምክንያት ሳይኖር የመተማመን መንፈስ ባለመኖሩ ብቻ ጦርነት ሊነሳ ይችላል። አንዱ በሌላኛው ላይ “የሃይል ዕርምጃ እወስዳለሁ” ሲል፣ ሌላኛውም “እርምጃ ሊወሰድብኝ ይችላል” እያለ ባለበት ሁኔታ ውስጥ የሚከሰቱ ነገሮች ወደ አልታሰበና ማለቂያ የሌለው ጦርነት ውስጥ ይገባል። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በድርድርና በውይይት ሊፈታ የሚችል ነገር ሀገራቱን ወደ አሰቃቂ ጦርነት ውስጥ አስገብቷቸዋል። በተመሣሣይ፣ በተለያዩ የዲፕሎማሲ ዕርምጃዎች መፍትሄ ሊሰጠው የሚችል ነገር “የአፀፋ እርምጃ እንወስዳለን” በሚል የፖለቲካ ግብዝነት ኢትዮጲያና ኤርትራ ዳግም ወደ ጦርነት ሊገቡ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
አንድ መንግስት በልማትና ዴሞክራሲ ረገድ የህዝብን ጥያቄ መመለስ ሲሳነው በጦርነት የሀገራዊ አንድነት መንፈስ ለመፍጠር መሞከሩ የታወቀ ነው። ለዚህ ሲባል የሚያደርጋቸውን ትንኮሳዎች በተለያዩ የዲፕሎማሲ ዕርምጃዎች መፍትሄ መስጠት ሲገባ በጦርነት መፍትሄ ለመስጠት መሞከር ፍፁም ስህተት ነው። በመሰረቱ፣ ጦርነት የሚሻ መንግስትን ጦርነት መግጠም ሌባን ለሌብነቱ እንደ መሸለም ነው።
በኢትዮጲያና ኤርትራ መካከል ትብብር ላለመፈጠሩ የሁለቱም ሀገራት መንግስታት እኩል ተጠያቂ ናቸው። የሁለቱ ሀገራት የፖለቲካ መሪዎች እርስ-በእርስ መተማመንና መነጋገር ስለተሳናቸው ብቻ የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች በጦርነት መከራና ሥቃይ ማየት የለባቸውም። በፖለቲካ መሪዎቻችን የዲፕሎማሲ አቅም ማነስ ወደ ጦርነት መግባት የለብንም።
በተለይ እኛ ኢትዮጲያኖች በድርቅ ምክንያት፤ 10.1 ሚሊዮን ሰዎች ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን በበቂ ሁኔታ መመገብ ባልቻሉበት፣ 400,000 ህፃናት ለከፍተኛ ለምግብ ዕጥረት በተጋለጡበት፣ ከ2.5 ሚሊዮን በላይ ህፃናት ትምህርታቸውን በሚያቋርጡበት ሁኔታ ውስጥ እያለን ሺህዎችን ደግሞ በጦርነት ለሞትና ቁስለት መዳረግ አንሻም። እነዚህ በሚሊዮን እና በሺህ የተጠቀሱት ቁጥሮች ብቻ ሳይሆኑ የሀገራችን ዜጎች ናቸው። ለዕለት ጉርስ ከመጨነቅ ባለፈ የተሻለ ሕይወት የሚገባቸው ሰብዓዊ ፍጡሯን ናቸው፡፡
ኤርትራዊያኖችም ቢሆን በአስገዳጅ ውትድርና የሚሰቃዩ፣ በስደት ከሀገር-ሀገር የሚንከራተቱ፣ …እንደ እኔና እናንተ የመኖር ተስፋ ያላቸው ሰብዓዊ ፍጡራን ናቸው። ሁላችንም በመሪዎቻችን አቅም ማነስ፣ ለውይይትና ድርድር ፍቃደኛ ባለመሆን፣ ችግሮችን በሰለጠነ የፖለቲካ መንገድ መፍታት ስለተሳናቸው ብቻ ወደ አሰቃቂ ጦርነት መግባት የለብንም።
*********
ጦርነት የኋላ ቀርነት ምልክት ነው፣ ተደራድረው አሣምንውና አምነው ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የማይችሉ ህዝቦችና ቡድኖች መለያ ምልክት ነው፡፡ ወይም አንደኛው ወገን ስግብግብ፣ ራሥ ወዳድ፣ ኋላቀርና በራሱ ብቻ የተያዘ ዚሆን ሌላኛው ወገን አማራጭ ሲያጣ ተገዶ የሚገባበት ነው፡፡ ግለሠቦችን የሚሣደቡ ለሰው ሀሣብ ክብር የሌላቸው ሠዎች ለአምባገነኖችና ለኋላቀሮች መጠላያ ዋሻዎች ናቸው ፡፡
ሌላው የሚለውን ከመራዳትና ከማስተካከል ይልቅ የራሡን ኋላቀር ሀሣብ በጭፍን እንድትቀበል የሚወተውትና ለማስገደድ የሚሞክር ሰውና/ ቡድን የሚበዛ ከሆነ የአቅም ማነሡ መገለጫ ጦርነት ይሆናል፡፡ ኋላቀርነቱን አይረዳምና በዚህም ይኩራራል፣ ሠው በመግደሉ ንብረት በማውደሙ ይፎክራል፡፡
ጀግና ለሠው ልጆች ችግር መፍትሄ የሚሠጥ እንጅ ሠወችን የሚገድል ሃሣባቸውን የሚያፍን አይደለም፡፡
Although I own a few older guns, my go-to weapon is a SIG-Sauer P-95&.It2#32;s hard for me to consider older guns for defence over what has come out since WWII, with the notable exceptions of the M1911, FN GP, and the Walther P.38.
Dear Belay .what you write is definitely true.Because ,there are so many internal problems as you mentioned. War at this time for Ethiopian is Bad News. why ? there are not answered questions in different part of Ethiopia .So this war is just to divert the attention of internal problems……
ጦርነት የአቅም ማነስ ምልክት ነው።
Dear Tehsome,
still,I agree. we should’t go in to a war. My argument is, what do mean by ” we didn’t do our best”. Suppose,two people quarreled for some reason. The one wanted to make peace and even sent model people like Oldies,,,,but the other refused to make peace and come to table.There fore,i don’t blame both of them equally. Let alone countries.You can take also husband and wife,due to disagreement and non-willingness of one them to make peace, divorce happens.I also don’t agree on using the word “equal” in such conditions, except in mathematics, equality has no sense. Every thing is relative to other. Thank you for understanding!!
Dear Belay,
We haven’t tried our best. If we did so, there would be peace and cooperation between the two countries. We Ethiopians have a lot to lose. So we shouldn’t be draged into war by any means. Mind you we have 10 million of our people face food shortage, which is twice the population size of Eritrea. Rather than bringing Isayas Afworki and his regime to the negotiation table, we are playing in to his hand. Whatever the case, we have to do that, otherwise the consequences are worse..
I am sure this article didn’t pass through Daniel Berhane’s edition. The author just picked one phrase from the MFA spokes person’s and made poor generalization and conclusion. The analogy of ethic Eritrea situation and wwi is far-fetched and makes no sense. No solid evidence was presented to support the supposed “argument” if it can be called one. The writing is also shallow and it is evident that the author lacks deep knowledge of the ethio Eritrea conflict and the subsequent events that unfolded over the last decade and more. I can confidently state that the author also is unaware of ethiopia’s policy towards Eritrea. One can easily tell this the way he understood the response of the mfa spokes person as he equated it with declaration of full scale war and he also failed to put the case from an international law perspective (right of self defence). I don’t know what he expect from the eth government? Wait and see when its citizen abducted in its sovereign territory? Also he treat both governments equally and as if Ethiopia did not seek for dialogue and peaceful resolution of the conflict. In any case, the writing is poor by any standard and it just repeats again and again about the need for nor going war and the need for dialogue. Not bad idea but doesn’t deserve to be an article to be posted in the Horn Affairs. I responded Coz I don’t expect such a poor and shallow piece from Horn Affairs.