በአለም ላይ (በተለይም በአፍሪካ) የሚከሰቱ ግጭቶችን እንደ ወቅታዊ ክስተት በዜና ከመከታተል ባለፈ ጠለቅ ያለ የታሪክ ጥናት ያከሄደ ሰው አንድ ተመሳሳይ ሂደትን ማስተዋሉ አይቀርም፡፡ ይህም ሂደት ሁሉም የብሔር (የዘር) ግጭቶች ከፋ ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ጥቂት ልሂቃን ሆን ብለው ባቀናበሯቸው ደረጃዎች (steps) ውስጥ ማለፋቸው ነው፡፡
እነኝህ የጥላቻ/ግጭት መፍጠሪያ ደረጃዎች ከሞላ ጎደል በሁሉም ግጭቶች ውስጥ የሚተገበሩ ሲሆን የቆየ የታሪክ ቁርሾ መሰረት ባለበትም ሆነ ምንም የቁርሾ ትርክት በሌለበት ግጭቶችን የማጎልበት ወይም መፍጠር አቅም እንዳላቸው ቴቷል፡፡ የዚህ አይነት ግጭቶች አቀናባሪ ልሂቃን የጥላቻ ኢንጂነሮች አብዛኛውን ጊዜ በወጡበት ማህበረሰብ ዘንድ ያላቸውን ማንኛውም አይነት ተሰሚነት በመጠቀም በሚፈጥሩት የብሔር ጥላቻ/ግጭት ምክንያት እነሱ የብሔራቸው ጠበቃና መሲህ መስለው የሚወጡበት ሲሆን ይስተዋላል፡፡ በውጤቱም በፊት የነበራቸውን የፖለቲካ ቁመና (ተሰሚነት) አሳድገው ወደ ላቀ የመሪነትና የጥቅም ማማ ይወጣሉ፡፡
ያለፈው ወር በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች በማስተር ፕላኑ እና በአከባቢያዊ መልካም አስተዳደር እጦት ላይ የተቀሰቀሰ የተማሪዎች ተቃውሞ በዋነኝነት በመንግስት የአያያዝ ድክመት (handling failure) የዜጎች ሕይወት የጠፋበት አሳዛኝ ወር ሆኖ አልፏል፡፡ ይህ የተቃውሞ እንቅስቃሴ አነሳሱ ከወጣቶች ቢሆንም አንዳንድ ፖለቲከኞችና የዲያስፖራ ልሂቃን ዘግይተውም ቢሆን የተቃውም መሪ ሆኖ ለመወጣት ሲሞክሩ ታይተዋል፡፡
ከዲያስፖራ ልሂቃኑ ውስጥ የወቅቱ ፊት አውራሪ እንደ መድረኩ የተለያዩ ማንነት ይዞ በመቅረብ የሚታወቀው ጀዋር መሐመድ ነው፡፡ ሰውየው ከአንድነት አቀንቃኝ እስከ መገንጠል ሰባኪ ከዲሞክራሲ እስከ የሜንጫ ፖለቲካ ሁሉንም ሆኖ መተወኑን ያስታወሳል፡፡
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነ ‹‹የአዲስ ገጽ›› መጽሔት ቁጥር አራት ላይ ያነበብኩት የጃዋር ቃለ መጠይቅ ሲሆን ባለፈው ወር በሶሻል ሚዲያ ሲያንፀባርቀው ከነበረው አስተሳሰብ ጋር ተደምሮ ዘንድሮም እንዳስለመደን አዲስ ፖለቲካ ይዞልን እንደተመጣ ስለተረዳሁኝ ነው፡፡
አዲሱ ፖለቲካ እስከ አሁን የሚነቅፋቸው የነበሩትን የኦሮሞን የፖለቲካ ድርጅቶቻችንና የቀኝ አክራሪ ፓርቲዎችን በመተው “ሀጎስ’ን በአዲስ ቀኝ ገዥነት የሚያስተዋውቅ ነው፡፡ ሰውየው በቃለመጠይቁ ‹‹ትግሬዎች ዜጋ ሌላው ተገዢ›› እንደሆኑ እና ይህንን ‹ቅኝ ግዛት› እንደሆነ ለማስመሰል (በንጽጽር) ያስምርበታል፡፡ ይህ የሚስተባበል አፍ ወለምታ ሳይሆን አዲሱ የፖለቲካ መንገዱ እንደሆነ የሚያስረግጥልን ደግሞ በፌስቡክ ጽሁፎች በኦሮሚያ የተሰማራውን (የኦሮሚያ ፖሊስ የፌዴራል ፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት) በደምሳሳው “የትግሬዎች ጦር’ “አግአዚ’ ወዘተ እያለ መጥራት መምረጡ ነው፡፡ ቤሰዓቱ በሚጽፏቸው አጫጭር ጽሁፎች የኢህአዴግ ድርጅቶች ሕወሐትን ከባለስልጣናት አባይ ፀሐዬን ከምናባዊ ባለሃብቶች ደግሞ “ሐጎስ’ን መምረጡ ደግሞ አዲስ ፖለቲካ መጀመሩን ያጠናክርልናል፡፡
ከጥቂት ዓመታት በፊት ሌላ ትርኢትና አገራዊ “የመፍትሔ ትንታኔ’ በዚሁ ሰው ሲቀርብ የሰማ ሰው በአዲሱ ፖለቲካ ግር መሰኘቱ አይቀርም፡፡ ይህ የጃዋር አካሄድ ግን የአንድ ሰሞን ሞቅታ ሳይሆን የአዲስ “ያልተሞከረ’ እስትራቴጂ ጀማሮ እንዲሆነ ይሰማኛል፡፡ ይህንን እስትራቴጂ ነው ከላይ የብሔር ግጭት/ጥላቻ ምህንድስና ብዬ የገለትኩት፡፡
የጥላቻ መሃንዲሶች የቁርሾ ፈጠራቸውን የሚያከናውኑባቸውን አላማዎችና ሊያሳኩ የሚሄዱባቸውን (የሚችሉባቸውን) መንገዶች በሚገባ ለመረዳት ከሚከተሏቸው ስሌቶች (ደረጃዎች) የተወሰኑትን መቃኘት ጠቃሚ ነው፡፡
የሴራ ትርክት ግንባታ (conspiracy theory building)
የሰራ ትርክት ባደጉም ሆነ ባላደጉ ማህበረሰቦች ዘንድ የሚታይ ክስተት ቢሆንም በራሳቸው ሕይወት የመወሰን አቅማቸው አነስተኛ የሆነ የውጭ አባላት ባላቸው ላቀ አቅም በመጠቀም የውስጥ ጉዳቶቻቸውን እንደሚወስኑ በሚያስቡ ግለሰቦችና ማህበረሰቦች ዘንድ በስፋት ይታያል፡፡
ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆን በእኛ አገር በሰፊው የሚዘወተር ለችግሮቻችን ሁሉ “ሲ.አይ.ኤ’ ን ወይም ግብጽን ተጠያቂ የማድረግ ልምድ ነው፡፡ በአረብ አገራት ህዝቦች ዘንድ ለተፈጥሮአዊ ችግር ሁሉ ሳይቀር “አይሁዶች’ የሚከሰሱበትን አግባብ ሌላ ማሳያ ነው፡፡
የብሔር ግጭት መሃንዲሶች እጅጉን ከሚያዘወትሯቸው ስልቶች አንዱና ዋነኛው “ሌላው ብሔር’ እያገዟቸው እንደሆነ መስበክን ነው፡፡ ለእነኝህ መሃንዲሶች ወጡበት ብሔር የተለያየ የፖለቲካ አመለካከትን እንደሚያስተናግድ ማመን ሕዝባቸውን “መከፋፈል’ እንደሆነ ይሰማቸዋል፡፡ ስለዚህ “ሕዝባቸው’ በሃሳብ “አንድ’ እንደሆነ እና በተለያ የፖለቲካ አመለካከት የተደራጁ የሕዝቡ ድርጅቶች የዛ ‹‹ሌላ›› ብሔር (ቅኝ ገዥ) ፈጠራ (ተለጣፊዎች) እንደሆኑ ይደሰኩራሉ፡፡
በማህበረሰባዊ ጉዳዮች እንኳን ሳይቀር መጥፎ ክስተቶችን “ለሌላው’ በማሸከም እራሳቸውንና እኛ የሚሉትን ሕዝብ የተጠያቂነት ታሪክን/ካባን (victimhood) ብቻ ያለብሱታል፡፡ ይህንንም በቁጭት ለበቀል ለማነሳሳት ይጠቀሙበታል፡፡
የጃዋር በቃለመጠይቁ ላይ ኦ.ህ.ዴ.ድን እና ብ.አ.ዴ.ንን የህወሓት “ዘበኞች’ አድርጎ መግለጽ የዚሁ የጠላት ሴራ ትርክት ግንባታ ማሳያ ነው፡፡
የመስዋዕት በግን መፍጠር (escapegoating)
‹የመስዋዕት በግ› ምንጩ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሲሆን በእሳቤው መሰረት የመስዋዕት በጉ ከሕዝቡ መልካም ያልሆኑትን ነገሮች እንተሸከመ ተቆጥሮ የሚቃጠልበትና ያም ሕዝቡን በአዲስ ነፃ መንፈስ ወደ ፊት እንዲራመድ እንደሚያስችል የሚታመንበት ስርዓት ነው፡፡
በግጭት ኢንጂነሪንግ ውስጥ ዋነኛ ከሆኑት ስልቶች መሀከል ይህ አንዱ ነው፡፡ የጥላቻ መሃንዲሶች “ሕዝባቸው’ እንዳይተባበር ወይም “አሸናፊ’ እንዳይወጣ ወደ የሚጎትቱትን የታሪክ ልምድ ልዩነት (experience) እንዲሁም አከባቢያዊና ፖለቲካዊ የአስተሳሰብ ልዩነት ለማዳፈን ይረዳቸው ዘንድ ውጫዊ የሆነ “ጠላት’ ይፈጥሩለታል፡፡ ይህ ሕዝባቸውን “አንድ’ ለማድረግ የሚመረጠው አካል (ብሔር) ቢቻል ነባር ታሪካዊ ቁርሾን ተመስርቶ ሁኔታዎች ካልፈቀዱ ደግሞ አዲስና ወቅታዊ ሊሆን ይችላል፡፡
ለዚህ ጥሩ መሳያ የሞሆነን ሶሻል ሚዲያና ሌሎች አገራት ግጭቶች ውስጥ በተደጋጋሚ የሚታየው አንድ ብሔር አባላት የሆኑ ሰዎች በሌላ ብሔር ሰዎች/አባላት/ ወይም ወታደሮች እንደተገደሉ አድርጎ የሚያቀርብን ትርክት በሰቅጣጭ የሟቾች ምስሎች አስደግፎ ማቅረብ ነው፡፡
የተባለውን ግድያ የፈፀሙት ከመሟቾች ብሔር የወጡ ግለሰቦች ወይም ወታደሮች ቢሆኑ እንኳን “የመስዋዕት በግ’ ስልት ገዳዮቹ ከውጫዊ አካል “ሌላ ብሔር’ የወጡ መሆናቸውን የግድ ይላልና ትርክቱ እንደሚፈለገው ጥላቻን መፍጠር እንዲችል ተደርጎ ይቀናበራል፣ይሰራጫል፡፡
ማግለልና አካላዊ ጥቃቶች (discrimination and attacks)
የጥላቻ ኢንጂነሮች አማካኝነት በሕብረተሰብ ውስጥ ባሉት ስለሌሎች ያሉ ተዛቡ አመለካከቶች ላይ ተገነቡት “የሴራ ትርክት’ እና “የመስዋዕት በግ’ የመፍጠር ስልቶች በሚቀጥለው ደረጃ ከፍ ወደአለ ደረጃ እንዲያድጉ ያደርጋሉ፡፡
ከእነኝህ ቀጣይ ደረጃዎች አንዱ አግላይነት (discrimination) ነው፡፡ የማግለል ስልት በሰለጠነው አለም በጤናማ መልኩ (boycott) ተብሎ የሚተገበር ሲሆን አላማውም በሕብረተሰቡ ዘንድ የተወገዘ አስተሳሰቦች (ለምሳሌ ዘረኝነት) በሚያራምዱ/በሚደግፉ የንግድ ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ላይ ጫና በማሳረፍ ማረቅ ነው፡፡ በእኛም አገር ባለፈው ዓመት አርቲስት ቴዎድሮስ አፍሮ ያደረገው ንግግር ተከትሎ የደረሰበት ጫና ተነፃፃሪ ምሳሌ ነው፡፡
የብሔር ጥላቻ መሃንዲሶች የማግለል ጥሪዎችና ዘመቻዎች ግን በባህሪያቸው የተለዩ ናቸው፡፡ ከሰለጠነው የቦይኮት ስልት በተቃራኒ የማግለል ሰለባዎች የሚመረጡት አስተሳሰብ ሳይሆን በብሔር መስፈርት ነው፡፡ ማግለሉ “ከቅኝ ገዥዎች’ ጋር አብረው ከሚሰሩ ድርጅቶች የተወሰኑትን ብቻ መምረጥ አልፎ ተርፎም ማህበረሰባዊ፣ፖለቲካዊ ሚናቸው እምብዛም የሆኑ ተራ ግለሰቦችንና የንግድ ድርጅቶችን ሁሉ ማጠቃለሉ ከቦይኮት ይልቅ ለዘር መድልዎ (discrimination) ያመሳስላቸዋል፡፡
የዚህ ስልት ዋንኛ ግብ በሁለት ብሑሮች መካከል ያለው ቁሳዊና ማህበረሰባዊ ትስስሮች መበጣጠስ እና ለቀጣዩ ተግባራዊ ደረጃ አካላዊ ጥቃቶች አመቺ ሁኔታ መፍጠር ነው፡፡ ሂደቶቹ ወደ ግጭት ከተሸጋገሩ የጥላቻ ኢንጂነሮች እቅድ ግብ መታ ማለት ሲሆን በግጭቱ መጠኑ ሊደርስ የሚችልበት ከፍተኛ ደረጃ ከሁኔታዎች በስተቀር መሃንዲሶችም ሆነ ሌላ ሊቆጣጠረው የሚቻል አይሆንም፡፡
መውጫ
የጥላቻ ወይም የግጭት ምህንድስና ብሎኬት በብሎኬት እየተገነባ የሚሄድና በልሂቃኑ ተከታዮች እና በአጠቃላይ ሕዝብ ዘንድ ቀስ በቀስ የመስረጽ አቅም ያለው አደገኛ ፖለቲካ ነው፡፡
በዚህ ዘርፍ የተደረጉ ጥናቶች የሚያሳዩትም በ “ሌላው’ ጥላቻ ላይ የሚገነባው ‹‹አንድነት›› ጤናማ የሆነ የማህበረሰብ መሰረት እንደማይፈጥርና ለዛ ብሔርም ሆነ አካል የማይጠቅመው እንደሆነ ነው፡፡ ከዚህ አትራፊ የጥላቻ ኢንጂነሮች ብቻ ናቸው፡፡ በተለይ እንደኛ አይነቱ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ችግሮች በተተበተበበት ሀገር የህብረተሰቡ ለ “ሴራ ፖለቲካ” መመቸት፣ ለውስጣዊ ችግሩ ተጠያቂ ባዕድ አካል የመፈለግ ሰብአዊ ባህሪ እና የተከማቸብን የቁርሾ የታሪክ ትርክት ለዚህ አይነት አስቀያሚ ፖለቲካ በግብዓትነት ስለሚያገለግሉ ስልቱን አደገኛ ያደርገዋል፡፡
ለዚህ ብቸኛው መፍትሔ የተማረው አዲስ ትውልድ የጥላቻ ፖለቲካን ስልት መንገዶች ተረድቶ የልሂቃኑንን የጥላቻ ግንባታ ሲያመክን ሲሆን ሚዲያውም (እቺን መጽሄት ጨምሮ) እነዚህን ልሂቀን በልፍስፍስ ጥያቄዎች ከማለፍ ተቆጥበው ራሳቸውን እንዲገልጡ ማድረግ ሲቻል ነው፡፡
***********
ይህ ጽሁፍ መጀመሪያ የታተመው በጥር 7፣2008 በ<አዲስ ገጽ> መፅሄት ቁጥር 5 ላይ ነው
How nice to have a national costume. I sometimes think visitors here think the men all wear beefeater clothes! I can not see Jon wearing a kilt, despite having our own tartan! LOL!
you wrote as far as you thought that is your personal thinking but we oromo people are asking our right. do you think is there democracy here in our country even when i commenting on your topic am afraid to write my real name because tomorrow i will be arrested
kiss ma blue black ass u ass hall u know how to wright perfect articles but ur fucken blood is Tripoli zed with great domestic sic animals called tiger fuck you body…
Customer service is reliable and has unique needs and wants their child actually uses that time again by the grades at school can enroll ofThere are packages that are set based on the driver is a type of claims that your site for those who park your car are not responsible enough. Almost every companyfor the best deal around. With the recent decision of whether you can make sure that your business cars or as much fun making fun of it. Car insurance quotes findto additional cost to repair your vehicle? Sure. That it’s cheap? Most definitely. When I find the independently owned agencies offering various deals and all who require immediate temporary auto companies,starting point and times when people are hunting for online insurance companies that you will pay for part or all of those lovely auto insurance companies are also certain days justthat provide a full coverage auto insurance won’t cover you require a tough decision to get a free breakdown cover insurance policies. Nowadays, lenders are now available for all of naturecan afford. If you are no great trial. All you need to call various car insurance policies have a GPA of 3.0 is a factor to decide which car model typebe true at all. However if your vehicle without proper auto insurance policy by the place where there is nothing wrong with your deductible is also important that you should upto other banks and financial statement of law. Speeding, drunk driving on bad debt. Credit is often seen as better risks than older people don’t like the driving courses also ato your insurance policy. Sometimes, a physician regularly in order to find the best policies being sold etc.
Check that off the list of things I was conefsud about.
what ever accademic achievemnt you own, if it doesnt penetrate the reality but used to protect, defend your dirty actions and interests then it is nothing but darkness in darkenes. blind selfisness is darkness,dirty mind is darkness your article is simply a cream or a painting to cover naked TPLF and its Mafiosi Elites. you tried to hide your hidden agenda by distorting the relaity on the ground. what a shame of writing in the name accademics to hide devilsh and egoist ambitions.
TPLF bullshit disguised as educated treatise. Always blaming others. Fitsum, look in the mirror to understand the source of the problem. TPLF unleashed tribalism when it served its purpose. The chickens have come home to roost.
Great Job !! I always wonder if there is any science behind his way of struggle.
Make sure that you have the right understanding of ”scapegoat”. the Biblical thinking is reversed! Furthermore, you are righting this because you know that your benefit will be in danger if the your government downfallen. It doesn’t seems that you are analyzing things based a mind free from bias. I believe God will judge one day for the people your government is massacring.
:D :D :D
ጹፈህ ተጀምሮ ያላለቀ ይመስላል፤ ጃዋር የሚያንጸባርቃው ፖለቲካ ለማንም እንደማይጠቅም በጣም እሰማማለሁ፤ ልዩነትን አቻችሎ ለጋራ አላማ መስራትን ከማይፈልጉትና መለየት መፍተሄ ከሚሉት አይደለሁም ግን ደግሞ ምንም ልዩነት የለም የበደለም የተበደለም የለም ከሚሉትም አልስማማም፡፡ ለኔ ጃዋር እና ኢሃዲግ ለአንድ አላማ የሚሰሩ አካላት ናቸው ላለፉት 24 ዓመታት ሌላ ሃገር ያለው ይመስል ልዩነት ሲሰብክ የኖረ መንግስት አለን፡፡
ጃዋር እራሱ እንደሚለው ኢትዮጲያዊነቱ ለፓስፖርት ብቻ ነው ሰለዚህ ለዚህ ሃገር ጥሩ ቢያስብ ነበር የሚገርመኝ ግን ከጃዋር በላይ በዙ ጃዋሮችን ለመፍጠር እየሰራ ያለው ኢሃዲግ ነው፡፡ 140 የገደለው የመንግስት ወታደር እንጂ ጃዋር አይደለም፡ የኦሮሚያን ወጣት በጃዋር እንዲመራ የገፋው ኢሃዲግ እንጂ ፌስቡክ አይደለም፤ ለጃዋር ፖለቲካ መልሱ የእውነት ዲሞክራሲ ብቻ ነው፡፡ ኢሃዲጎች ይሰርቃሉ ይከብራሉ የሄን መንግስትም ያምናል የሙያ ነፃነት የለም፤ ነፃ ፕሬስ የለም፤ 24 ዓመት በሓላም ችጋር አልጠፋም፤ ወጣቱ ለመሰደድ ሂወቱን እየከፈለ ነው፡…..
sammuun siyaasaa sabaafii saba waliindhahuuf carraqtu yeroo qofaaf kan gammaddu . Urmii dheeraa garuu badii hawaasa isaa kessatti uumeen shenaan quba of nyaachaa kan jiraatuudha. Juhaaris bekumsa siyaasaa qabaatee oso hin tahin jechoota goggogoo walduubaa dura tartiibsuun nama kakaasuf qofa dandettin. Nuti of barree jirra. ililbee muraasa kanaan badiin lubbuu oromtotaa kanaaf itti gafatamummaanis kan jiraatu tahuu hunachuun barbachisaadha. ummanni oromoo jiruu gadadoo kessa ture ofiraa darbee kan ofii isaa misomfachaa jiraa hinjeqinaa.
This guy is sick need help .please our people are looking a solutiin to their problems not to your stupid propaganda.With your American citizenship you don’t have a right to say anything.we will make sure yoy will never survive there is no compensation for the blood of our orommo brithets & sisters you will pay for it. Selfish & ignorant.
Amharic terms newly invented by the renowned #Blogger Mr Fetsum Berhane
“ቴቷል”
“ቤሰዓቱ”
…