ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግል 10 ዓመታ ካስቆጠረ በኋላ፤ በ1977ዎቹ የፖለቲካ አመራር የሚሰጥ አደረጃጀት ማርክሳዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ(ማሌሊት) በሚል ስያሜ እንደመሠረተ ይታወሳል፡፡
ያ አደረጃጀት ዓለም-አቀፋዊውን የአሰላለፍ ለውጥ ተከትሎ ከ1983 በኋላ እንዲቀር መደረጉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በአብዛኛው ሕዝብ እምብዛም አይታወቅም፡፡
ይሁን እንጂ ህወሓት ከ1970ዎቹ አጋማሽ በኋላ ላሳየው የወታደራዊ እና ድርጅታዊ እመርታ ምክንያቱ የማሌሊት ምሥረታ ያስከተለው የርዕዮተ-ዓለም ጥራት ነው ብሎ ያምናል፡፡ በአንጻሩ የቀድሞው የድርጅቱ አመራር ገብሩ አሥራት በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ፡- በወቅቱ የተገኙት ለውጦች ያለማሌሊት ሊከሰቱ የሚችሉ የአደረጃጀት ለውጥ ውጤቶች ናቸው የሚል ሀሳብ አንስተዋል፡፡
ባለፈው ሰኞ ጥር 30-2007 ቃለ-መጠይቅ ያደረግንላቸው ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሰኤ ካቀረብነው ጥያቄዎች አንዱ ማሌሊትን የተመለከተ ነበር፡፡
ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት እና ማሌሊት ሲቋቋም ከመጀመሪያዎቹ 9 የፖሊት ቢሮ አባላት አንዱ የነበሩት እንዲሁም የህወሓት ሠራዊት ቺፍ ኦፍ ስታፍ የነበሩት ጻድቃን፤
* የማሌሊት ምሥረታን እና በሕወሓት መዋቅር ላይ የነበረውን ፋይዳ ያብራሩ ሲሆን አያይዘውም
* የህወሓትን ወታደራዊ ስትራቴጂ ጽንሰ-ሀሳቦች፣
* ከደርግ 603ኛ ኮር ጋር በሽረ የተደረገውን ውጊያና ተዛማጅ ታሪካዊ ሁነቶችን እንደሚከተለው አብራርተዋል፡፡
[እስከ 1993 የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማጆር ሹም የነበሩት ሌፍተናንት ጄኔራል ጻድቃን፤ የህወሓት-ሻዕቢያ ግንኙነት፣ የ1977ቱ ረሀብ፣ በኤርትራ ወረራ ወቅት የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ሚና፣ የቀድሞው ሠራዊት መበተን እና ሌሎች ዐብይ ርዕሰ-ጉዳዮች እንዲሁም ስለራሳቸው ለቀረቡ ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሾች በተከታታይ እናቀርባለን]
——
Watch Video below.
*************
ááááµ áá°á¨á³á áá³á°á«á ááᥠá¥áá³áᣠááá á¥áá¥á á¨ááá áá« á«áá£á áá á¨áµáá«á á áᥠá¨áµáá á£áá¤áµ á¥á«á ááááµáá áá® á¨ááá á á°á°á³á°á á«áµááá¡á áµ? á ááµ á áµá°á³á°á á¨áááááá á áᥠáµáá½ á¨ááá°á á¨á®á á áá¡á á¥áá½áá áááµ á¨áá áµá ᢠá áááµ á«ááµ á¨áá¨á¥á«á¸á á¨ááááµ áááá½ á³áá®á½ á áá± ááá«á á»áµáá áá ᢠI didn’t say thanks when I had a chance to tell you in person but I will say it now tsadqan thank you for your contribution to success of TPLF .