በአቶ ትእግስቱ አወሉ የሚመራው የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤውን ባለፈው ቅዳሜ በቶፕ ቪው ሆቴል አካሂዷል።
በጠቅላላ ጉባኤው 239 አባላት ተጠርተው 193ቱ ተገኝተዋል። ይህም ከግማሽ በላይ በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዳቸውን በጉባኤው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አቶ ትዕግስቱ አወሉ ተናግረዋል።
ሶስት የፓርቲው አባላት ማለትም አቶ ትዕግስቱ አወል፤ አቶ ጋሻው አሰፋና አቶ ደረጄ ሚሊዮን ለፓርቲው ፕሬዝዳንትነት በእጩነት ቀርበዋል፡፡ ከአዳማ የፓርቲውን ቅርንጫፍ በመወከል የተገኙት አቶ ጋሻው አሰፋ ከውድድሩ ራሳቸውን ያገለሉ ሲሆን ሁለቱ እጩዎች በሚስጥር በተካሄደ የድምፅ አሰጣጥ ተወዳድረዋል፡፡
አቶ ትዕግስቱ አወል ከተሰጠው ድምፅ 136 ሲያገኙ አቶ ደረጄ ሚሊዮን ደግሞ 48 ድምፅ በማግኘታቸው አቶ ትዕግስቱ ፓርቲውን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ዳግመኛ ተመርጠዋል፡፡
ጠቅላላ ጉባዔው ለኦዲትና ኢንስፔክሽን የቀረቡለትን 10 እጩዎች አወዳድሮ 7 አባላትን መርጧል፡፡ በተመሳሳይ ለብሔራዊ ም/ቤት አባልነት 57 ዕጩዎች ቀርበውለት በ55ቱ ላይ ድምፅ ሰጥቷል፡፡
የጠቅላላ ጉባኤውን እና አጠቃለይ ውሳኔዎቹን ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንደሚያቀርቡም አቶ ትዕግስቱ ተናግረዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ ጉባኤ ላይ ተወካዩን አልላከም፡፡
በሌላ ወገን ያለው የአቶ በላይ ፈቃዱ ቡድን ደግሞ ምንም አይነት ጠቅላላ ጉባኤ አላካሂድም በሚለው አቋሙ እንደፀና ነው።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለቱ የፓርቲው አመራር ነን የሚሉ ቡድኖች ችግራቸውን በጠቅላላ ጉባኤ ፈተው እንዲመጡ የሰጠው ተጨማሪ የሁለት ሳምንት ጊዜ የፊታችን ማክሰኞ ይጠናቀቃል።
******
naked, crude and laughable gimmick by the regime. This is windfall to those who advocate violence as a means of bringing change in Ethiopia. I cant for the life of me understand why the ruling party resorts to this kind of violations while it can safely steal the election cards with the help of its own so called election commission. That would have been a little less blunt.