በአንድነት ፓርቲ ውስጥ በተፈጠረው ውዝግብ ግንባር ቀደም ሚና ያላቸው አቶ አየለ ስሜነህ የአሰላለፍ ለውጥ አደረጉ፡፡
የእነትእግስቱ አወልን ቡድን በማደራጀት ቀዳሚ ሚና የነበራቸው አቶ አየለ፤ ሰልፋቸውን ቀይረው የነበላይ ፈቃዱን ቡድን መቀላቀላቸውን ትላንት የአንድነት ልሳን ለሆነው ለ‹‹ፍኖተ-ነፃነት›› በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡
አቶ አየለ የቅሬታቸው መነሻ የሆኑት ጉዳዮች ያልተመለሱ ቢሆንም ወቅቱ የምርጫ በመሆኑ እና ፓርቲውን ከአደጋ ለማዳን ሲሉ የአሰላለፍ ለውጥ እንዳደረጉ ገለጸዋል፡፡
‹‹ፍኖተ-ነፃነት›› የለቀቀውን የአቶ አየለ ስሜነህ መግለጫ ቪዲዮ ከታች ይመልከቱ፡፡
***********