በአሶሳ ዞን ታጣቂዎች ዘጠኝ ሰዎች ገደሉ

ትላንት ሚያዚያ 7/2006ዓ.ም ማለዳ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ በነበረ ፒካ አፕ መኪና ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በሰው ህይወትና አካል ላይ ጉዳት መድረሱን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ገለፀ፡፡

ጽ/ቤቱ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በተሽከርካሪው ላይ ጥቃቱን ያደረሱት ከንጋቱ 12 ሰዓት ተኩል አካባቢ፣ የክልሉ ርዕሰ መዲና ከሆነው ከአሶሳ ከተማ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገ‚ው ሸርቆሌ ወረዳ ልዩ ስሙ ጠይባ ከሚባለው አካባቢ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ በስድስቱ ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ጥቃቱን ፈፅመው የተሰወሩ ግለሰቦችን አድኖ በህግ ፊት ለማቅረብ የህግ አስከባሪ ኃይሎች ክትትል በማድረግ ላይ መሆናቸውን የገለጸው ጽ/ቤቱ በጥቃቱ ተጠያቂ የሆኑትን ግለሰቦች ማንነት ለማጣራትም ምርመራ መጀመሩን እና የምርመራውን ውጤት የሚመለከቱ መረጃዎችን በወቅቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡

********

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

more recommended stories