(ጌትነት ምህረቴ)
ባቡር ከየብስ የትራንስፖርት በዋጋ ርካሽ እንደሆነ ይነገራል። ፍጥነቱም ከተሽከርካሪ ይበልጣል። በአንድ ጊዜ ብዙ ሰዎችን ሆነ ሸቀጦችን በመጫን የማጓጓዝ አቅም አለው። በተለይ የባቡር ትራንስፖርት ለታዳጊ ሀገሮች የመገንቢያው ወጪ ከፍተኛ ቢሆንም ተመራጭ የትራንስፖርት ዘርፍ እንደሆነ የሚታወቅ ነው። የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ዕድገት ተከትሎ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በእጅጉ እየጨመሩ ይገኛሉ። የማዕድን ምርቶችን በተሽከርካሪዎች ብቻ ማጓጓዝ ወጭው ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ረጅም ጊዜ ይወስዳል። ይህም የሚያ ሳየው ከኢኮኖሚው ዕድገቱ ጋር የተጣጣመ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚያስፈልግ አጠያያቂ ያለመሆኑን ነው።
መንግስትም ይህን በመገንዘብ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ እንዳስቀመጠው በሀገሪቱ በሶስት ኮሪደሮች በአምስት መስመሮች ሁለት ሺ 395 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የባቡር ኔት ወርክ ለመገንባት የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች ተነድፈው ለመገንባት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። አንዳንዶቹ ፕሮጀክቶች ከዕቅዱ አኳያ ቢዘገዩም በአንፃሩ ደግሞ ግንባታቸው የተጀመረ ፕሮጀክቶች አሉ። ከተጀመሩት መካከል የአዲስ አበባ ቀላል የባቡር መስመርና የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር ግንባታ ይገኙበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ዝርዝር የዲዛይን ጥናታቸው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙም ፕሮጀክቶች ይገኛሉ።
ከእነዚህ መካከል አንዱ ከአሳይታ-ታጁራ ድረስ የሚዘረጋው የ260 ኪሎ ሜትር የባቡር ፕሮጀክት ነው። ለእዚህ ፕሮጀክት ማስፈፅሚያ የሚውል ገንዘብ የህንድ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ በብድር ለመስጠት ስምምነት ላይ ተደር ሷል። ባንኩ ብድሩን ለመስጠት በመስማማ ቱም የመጀመሪያውን 300 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ብድር ማስገኘት የሚያስችለውን የብድር ስምምነት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተፈራርሟል።
ከአሳይታ ታጁራ ድረስ የሚዘረጋው የባቡር መስመር ከመቀሌ-ታጁራ ሊዘረጋ የታቀደውን የባቡር መስመር አንድ ክፍል ነው። የባቡር መስመሩ ከሀገራችን ወደ ጂቡቲና ከጅቡቲ ወደ ሀገራችን የሚጓጓዙ ሸቀጦች በዝቅተኛ ዋጋና በብዛት በማጓጓዝ ለነዳጅ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ መቀነስ ያስችላል። እንዲሁም የአፍሪካ ሀገሮችን በባቡር መስመር ለማገናኘት ከተነደፈው ከጅቡቲ-ዳካር የባቡር መስመር አካል በመሆን በአፍሪካ አገሮች መካከል የኢኮኖሚ ትስስር በመፍጠር ረገድም የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።
ከመቀሌ -ታጁራ ድረስ ያለው ርቀት 683 ሲሆን ከዚህ ውስጥ 160 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር በጅቡቲ ግዛት ውስጥ የሚዘረጋ ነው። የባቡር መስመሩ ባለ አንድ ሀዲድ ሆኖ በሰዓት 120 ኪሎ ሜትር ያህል ፍጥነት ይኖረዋል። ለፕሮጀክቱ አጠቃላይ ያስፈልጋል ተብሎ ከተገመተው አንድ ቢሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ውስጥ 300 ሚሊዮን ዶላር ብድር የህንድ መንግስት ሰጥቷል። የፕሮጀክቱ ዝርዝር ጥናት ሲጠናቀቅ ተጨማሪ የ300 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚሰጥ በህንድ መንግስት በኩል ቃል ተገብቷል። የፕሮጀክቱ ቀሪው የገንዘብ ልዩነት በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው።
ከህንድ መንግስት በብድር የተገኘው 300 ሚሊዮን ዶላር በዓመት አንድ ነጥብ 75 በመቶ ወለድ ይከፈልበታል። ከአምስት ዓመት የችሮታ ጊዜ በኋላም በ15 ዓመታት ውስጥ ተመልሶ የሚከፈል ነው። ብድሩ ከኢትዮጵያ የብድር ስትራቴጂ ጋር የተጣጣመ ከመሆኑ ባሻገር አነስተኛ ወለድ የሚከፈልበት ነው። በዕድገትና ትራንስፎ ርሜሽን ዕቅድ ከተቀመጡት የባቡር መስመር ግንባታ ፕሮጀክቶች ውስጥ ብድሩ ከአሳይታ እስከ ታጁራ ድረስ ያለው የባቡር መስመር ግንባታ ለፍፃሜ እንዲበቃ የሚያስችል ነው። የባቡር መስመር ግንባታው ሲጠናቀቅም የወጪና የገቢ ምርቶችን በፍጥነትና በአነስተኛ ወጪ በማጓጓዝ ረገድ የጎላ ሚና ይኖረዋል። በግንባታ ሂደትም ለብዙ ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራል። በዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፈጠርም ይረዳል ሲሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ወንድሙ ገዛኽኝ ይገልፃሉ። ይህን መሰረት በማድረግም የረቂቅ የብድር ስምምነቱን ማፅደቂያ አዋጁን ምክር ቤቱ እንዲያፀድቀው ጠይቀዋል። የምክር ቤቱ አባላትም ብድሩን በተመለከተ ዝርዝር ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከልም የባቡር ግንባታው ምን ያህል አዋጭነቱ ታይቶ ነው እስከ ጅቡቲ ድረስ የባቡር ሀዲድ የምንገነባው? በሁለቱ መንግስታት በኩል ምን አይነት ስምምነት ተደርሶ ነው?፤ የባቡር መስመር ግንባታው የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከመፍጠር አኳያ አስተዋፅኦ ይኖረዋል?
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስተር አቶ ሱፊያን ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሲሰጡ እንዳሉት ይህ የባቡር መስመር የሀገራችን ሰሜንና ሰሜናዊ ምስራቅን ከማገናኘቱ ባለፈ ጅቡቲ ውስጥ ወደሚገኘው አዲሱ የታጁራ ወደብ ድረስ የሚዘረጋነው። ይህም ኢትዮጵያ ይህን ወደብ በመጠቀም ወደ ውጭ የምትልካቸውን የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለማጓጓዝ ያስችላል። እንዲሁም ሀገሪቱ ወደ ሀገር ውስጥ የምታስገባቸ ውን ሸቀጦች በቀላሉ ለማጓጓዝ የሚያስችል ነው። በተጨማሪም በአፋር ክልል አካባቢ የተገኘውን የፖታሽ ሀብት ለውጭ ገበያ ለማቅረብና መስመሩ በሚያልፍባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ማለትም ለትግራይ፤ ለአማራ ለአፋር ነዋሪዎች እና ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ተጓዦች የባቡር ትራንስፖ ርት አገልግሎት የሚሰጥ ነው ። የሚዘረጋው የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ በመሆኑ ለጭነት ተሽከርካሪዎች ነዳጅ እና መለዋወጫ ይወጣ የነበረውን ወጪ ያድናል። ይህም ገንዘብን ለሌላ ልማት በማዋል የኢኮኖሚ ዕድገቱን እንዲፋ ጠን ያግዛል።
የባቡር መስመር ግንባታ ፕሮጀክቱ የተለያዩ ክፍሎች አሉት። አንዱ ሀዲድ መዘርጋት ሲሆን ሌላው ደግሞ የባቡር መስመሩ የራሱ የሆነ ባለ 123 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመርና የመገናኛ መስመር እንዲሁም የመቆጣጠሪያ ስርዓት ይኖረዋል። የባቡር መስመሩ በሚያልፍበት አካባቢዎች በሚገኙ 37 ከተሞች ጣቢያዎች ይኖሩታል። የባቡሩ መስመር ከተሰራ በኋላ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በድሬዳዋ አድርጎ ጅቡቲ ድረስ በሚዘረጋው የባቡር መስመር ጭምር ኢትዮጵያና ጅቡቲ ቀደም ሲል እንደነበረው አካሄድ ሳይሆን የተለየ ስምምነት አድርገዋል። ሀዲድን በተመለከተ ጅቡቲዎች እስከ ራሳቸው ወሰን ድረስ ራሳቸው ያስተዳድራሉ። ነገር ግን ሀዲዱ ከተሰራ በኋላ ማጓጓዙን በተመለከተ ሁለቱ ሀገሮች በጋራ ኩባንያ ያቋቁማሉ። ኩባንያው የንግድ ኩባንያ ነው። በዘመናዊ የኩባንያ አሰራር የሚመሰረትና ሁለቱ መንግስታት የሚወኩሉት ድርጅቶች የሚያስተዳድሩት ይሆናል። ኢትዮጵያን የሚወክለው ድርጅት ተግባራዊ እንቅስቃሴ የጀመረው የኢትዮጵያ የባቡር ኮርፖሬሽን ነው። በጅቡቲ በኩልም እንዲሁ ተመሳሳይ አይነት ድርጅት አቋቁመዋል።
መንግስትን ወክለው እነዚህ ሁለት ኩባንያዎች የጋራ ኩባንያ ፈጥረው ያንን ኩባንያ ያስተዳድራሉ። የኩባንያው ሀብትና ዕዳ የሚወሰነው ሁለቱ ሀገሮች በሚያዋጡት ገንዘብ ይሆናል ይላሉ። «በእኛ ግምት አብዛኛው እስከ 90 በመቶ ሊሆን የሚችለው የኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፍነው ይሆናል ብለን ነው የምንገምተው።ለስራው እንዲመችና ለማስተባበር እንዲቻል የኢትዮጵያ መንግስት ድጋፍ አድር ጎልን አስተባብሮ ይስራ የሚል ጥያቄ ከእነሱም በኩል ስለቀረበና በእኛም በኩል ተቀባይነት ስላገኘ በጋራ እየሰራን ነው። በዚህ መሰረትም ከጅቡቲ ጋር የጋራ ኮሚቴ አቋቁመናል። በእነሱ በኩል ያለውን ወጪ እነሱ ይችላሉ። በእኛ በኩል ያለውን ወጪም እኛ እንችላለን ነው» ያሉት አቶ ሱፊያን።
የመቀሌ-ታጁራ የባቡር መስመር የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ሀገሮችን በባቡር መስመር ለማገናኘት ከነደፋቸው ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የጅቡቲ ዳካር የባቡር መስመር አካል ነው። ይህም ሀገሪቷ ከአፍሪካ ሀገሮች ጋር የኢኮኖሚ ትስስር እንድትፈጥር ያስችላታል። የዚህ ፕሮጀክት የአዋጭነት ጥናት የተጠናቀቀ ሲሆን በዚህ ጥናት መሰረት ከመቀሌ እስከ ሀራ ገበያ ፤ ከሀራ ገበያ እስከ አሳይታ እንዲሁም ከአሳይታ እስከ ታጁራ ድረስ ያለው የባቡር መስመር በሶስት ከፍሎች ተከፋፍሎ የሚገነባ ይሆናል። ግንባታውን ለመጀመር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ከምክር ቤት ለቀረቡት ጥያቄዎች ሚኒስትሩ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ረቂቅ የብድር ስምምነት ማፅደቂያ አዋጁን ምክር ቤቱ አፅድቆታል።
የባቡር ትራንስፖርት የምርት ግብዓቶችንና ምርቶችን በአነስተኛ ዋጋ በአጭር ጊዜ በገፍ ለማማጓጓዝ የሚያስችል ተመራጭ ትራንስፖርት ነው። በዕድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅዱ ሀገራዊ የባቡር መስመር ዝርጋታው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ቢገኘም ከዕቅዱ አንፃር እስካሁን ድረስ ተግባራዊ ስራ ያልተጀመረባቸው ፕሮጀክቶች እንዳሉ በመገንዘብ በቀሪ ሁለት ዓመት የዕቅድ ዘመን በዘርፋ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ ስራ ማከናውን ከመንግስት የሚጠበቅ ተግባር ይሆናል።
*************
*Originally published on Addis Zemen newspaper.
Tendaho Sugar factory project started in 2006. Now it is now more than 7 years, it hasn’t yet started production. The country is spending several millions of dollars every year to import sugar.
In 2007 Indian & Ethiopian government signed a $ 640 million dollar loan to build three sugar factories. The agreement states that 85% of the project design, work, consultations, construction, and material.. has to be done by Indian companies and suppliers. Ethiopian government also injected a lot of foreign currency into this project. Here we are after 7 years, it should have been completed in 2009, the project has started to crack, outdated, becoming old, & it’s also lost opportunity cost without producing a single benefit to Ethiopia. Ethiopia is losing billions of dollars in inflation, poor quality of Indian suppliers & contractors, interest payment…
Ato Abay Tsehaye is the main responsible person in the sugar industry. If he can’t delivery the country dream to be self sufficient and to make sugar one of the export commodity, he has to resign from his position or the government has to take the same measure as it did to the former justice minister. Otherwise, it seems the government takes measures only based on the official’s ethnicity.
This kind of officials have to evaluate their stand. Are they stranding for the interest of Ethiopian or Indian companies?
@ Danielll & Mittal
I think the Ethiopian government knows well about the highly corrupted reputation of Indians… unless they are using their easiness intentionally for billions if not millions of dollars in the expense of this and the generations to come,
hadn’t we enough damage already? their bad corrupt products, selling lands with size of countries…. list goes on
who really is caring for this country and this poor people unless the government does?
I am saying, “CONTRACTS OF ALMOST ALL OF THE PROJECTS IN ETHIOPIA THIS TIME ARE NOT TRANSPARENT, WAY FAR INDEED… let alone to the public even to most of the government people” … there are just FEW CARD PLAYERS!!! amlak libona yistachew!
The one financed by the Indians if done by Indian contractors you can forget it. It will take tem ten years. This are highly corupt and people and has bee proven all over the world most Indian contractors form IT too construction have been listed at world Bank not to work on the Bank funded projects… Even Kenay is geting tiered of this scruples Indian contracturs and recently denied many Indian companies not to get involved even as subcontractors on two huge projects in LAmu and a niroby housing projects…. I mean even as suppliers..
Indian Exim bank gave the loan to push the interest of Indian companies. Many Indian companies track record in Africa is not encouraging. They provide poor quality materials and equipments to any contract they involve in.
They also encourage and expand corruption culture in Africa. Indian companies have been placing a lot of damage to Ethiopia’s economy too. They have been providing poor quality and second hand transformers to EEPCo by conspiring with corrupted officials. This transformers are one of the reasons for continuous blackouts in Ethiopia. This blackouts costing Ethiopian companies and govt millions of dollars. Ethiopians are forced to pay the principal loan plus interest for materials worth nothing.
There is also a huge sugar factory in Afar region. This factory funded by Ethiopian govt and Indian Exim bank. The project supposed to be complete many years ago. It has been built by unqualified Indian companies. They brought many Indian workers even though there are many qualified Ethiopians out there. The Indian laborers get paid more than five times their Ethiopian counterpart even if they do the same kind of jobs. This is totally a racist practice performing by Indian companies against Ethiopians. Awhile back Ethiopian Reporter news paper wrote a well investigated article on this issue. These companies hasn’t yet completed the project based on the contract due date. They are discriminating locals. Furthermore, they are highly costing the country economy by using poor quality materials and machines. The poor Ethiopian tax payers and their children would be the one force to pay the loan with its interest to under performing and corrupted Indian companies.
The Ethiopian Ambassador in India might be one of the reason for this mess. When she was minster of Education, she used to pay Ethiopian university lectures 10 times less than the Indian counterparts, and she was publicly defended her unfair practice against Ethiopian Scholars.