* ዶ/ር ነጋሶ….. <አማራም ቢሆኑ ውስጡ ገብቼ አንድነትን አጠናክራለው> የሚል አቋም አላቸው።
* አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞነት አለባቸው ይባላል። ኦሮሞነት ስላላቸው የኦሮሞን ታሪክና ባህል አላቸው ማለት ግን አይደለም
* ቡልቻ “አማራ” የሚለውን ቃል ተጠቀመ ብለው [አንድነቶች] ሊከፋቸው አይገባም። ታዲያ እኔ ምን ብዬ ልግለጣቸው? እዛ ያሉትን እኔ የማውቃቸው በአማራነታቸው ነው።
* በአንድነት ውስጥ ያሉ አማራዎች ግን የጀነራል፣ የሀገረ ገዢ፣ የአምባሳደር የአስተማሪና የሲቪል ሰርቪስ ልጆችና የልጅ ልጆች ናቸው።
* አፄ ቴዎድሮስም ቢሆን በጀግንነቱና ወንድነቱ እኛ ኢትዮያውያን ብቻ ሳይሆን መላ አፍሪካ ሊኮራ ይችላል። ነገር ግን እንደ ኦሮሞና ደቡብ ከእሳቸው ጋር አንተዋወቅም።
* አቢሲኒያ የሚባል ሀገር ነበር። ምናልባት ሶስት ሺው ከዚያ ጋር ተያይዞ ሊገለፅ ይችላል። የዛሬው ደቡብ፣ ምስራቅ ምዕራብ አቢሲኒያ አልነበረም።
* [አፄ ምኒልክ ወኪሎቻቸውን በመላክ] ዛሬ የምናውቃትን ኢትዮጵያን ፈጥረዋል።…..ነገሩ ሁሉ የሆነው በጉልበት ነው። በእርግጥ ጀርመንም፣ ጣሊያንም ይሄው ልምድ በመኖሩ በዚህ ላይ እኔ ቅሬታ የለኝም።
የቀድሞ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ሊቀመንበር አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ከሰንደቅ ጋዜጣ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ፡፡
ሰንደቅ፡- በአሁኑ ወቅት የመድረክና የአንድነት ፓርቲ ግንኙነት እንዴት ይገመግሙታል?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- በመጀመሪያ ልዩነት የተነሳው አንድነት መድረክን እገመግማለሁ ብሎ መነሳቱ ነው። በእኔ እምነት አንድነት ፓርቲ መድረክን ሊገመግም አይገባውም። ምክንያቱም አንድነት እራሱ የመድረክ አንዱ አካል ነው። መድረክ በራሱ እንጂ በሌላ ፓርቲ ሊገመገም አይገባም። አንድ አባል ፓርቲ አፈንግጦ ወጥቶ ከውጪ እንደሌለ ፓርቲ መገምገም ትክክል አይደለም።
ሰንደቅ፡- ግምገማው መድረክ ይበልጥ እንዲሰራና እንዲሻሻል በማሰብ መካሄዱን የአንድነት ፓርቲ ሲገልፅ ቆይቷል። ከዚህ አንፃር ግምገማውን ከበጎ ጎን ማየቱ ተገቢ አልነበረም?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- በእርግጥ ትክክል ነው። ነገር ግን ብቻቸውን ሳይሆን ከቀሩት የመድረክ አባል ፓርቲዎች ጋር በመሆን ተመካክረው መገምገም ይገባቸው ነበር። አሁን የሌሎቹ ፓርቲዎች አስተያየት ባልተካተተበት ሁኔታ ነው ገመገምን ያሉት። ድምፃቸውም የተሰማው የገምጋሚዎቹ ብቻ ነው።
ሰንደቅ፡- የመድረክን እንቅስቃሴ በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች አንድነት መድረክን የገመገመው ከመድረክ ጋር አብሮ መቀጠል አዋጪ መስሎ ስላልታየው ነው ይላሉ፤ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- መድረክን ስናቋቁም እኔም ነበርኩ። ኦፌዴንን ይዤ ነው ከጓደኞቼ ጋር መድረክ ውስጥ የገባሁት። ወደ መድረኩ የገባነውም ተማክረን ነበር። የምክራችን የጀርባ አጥንት የነበረው ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር በአንድነት እንድትኖር ከተፈለገ ወገኖቿን ሁሉ ይዛ መቀጠል አለባት። ይህ ማለት ቤት አለምሰሶ እንደማይቆም ሁሉ፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁሉም ካልተባበሩ እና ካልደገፉዋት ኢትዮጵያ ሀገር ልትሆን አትችልም። እና በወቅቱ በዚህ ላይ መክረን፣ ዘክረን፣ ገብቶን፣ ሁላችንም አምነንበት ነበር። ኢትዮጵያ “ኢትዮጵያ” ተብላ በምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ታላቅ ሀገር ሆኗ እንድትኖርና እንድትከበር የሁሉም ሕዝብ ትብብር፣ አንድነትና መልካም ስሜት እንዲሁም ፍቅር መኖር አለበት። አለበለዝያ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አትኖርም። ስለዚህ መድረክን የመሰረቱት ፓርቲዎች አንድነትን ጨምሮ ይሄንን በደስታ ተቀብለው፤ “ያላችሁት ትብብር መቶ በመቶ አስፈላጊ ነው” ብለው መድረክን ጀመርነው። አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ ተስፋ መድረክ ነው። አንድ ፓርቲ ተነስቶ ገንዘብ ከውጪ መጥለቶለት፣ ከመሬት ተነስቶ ምንም ቢያደርግ አይሆንለትም። ሁሉም ሕዝብ የደገፈው መንግስት ነው መቆም የሚችለው። ሕዝቡ የደገፈው ማለት የአብዛኛውን ሕዝብ ድምፅ ያገኘ ማለት ነው። በአምባገነንነት ቢሆን አይችልም። አምባገነንነት ከቀጠለ ነገም አንድ ሰው በግድ ልክ እንደ አፄ ቴዎድሮስ አይነት ተነስቶ ልግዛ ሊል ይችላል።
ሰንደቅ፡- አፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ አንድነት መድከማቸው በታሪክ ይነገራል። እርስዎ ይሄንን እንዴት ነው የሚረዱት?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- አፄ ቴዎድሮስ እኔ የምረዳበት መንገድ የተለየ ነው። አፄ ቴዎድሮስ ለእንግሊዟ ንግስት የሚፅፉትን ደብዳቤ ብታይ ለኢትዮጵያ አንድነት መቆማቸውን እንድትጠራጠር ያደርግሃል። አፄ ቴዎድሮስ የዛሬውን ምስራቅ፣ ደቡብና ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚያውቁት አይመስለኝም። በእኔ እምነት በኢትዮጵያ ታሪክ እስከዛሬም ቢሆን ኢትዮጵያን አንድ አደርጋለሁ ብሎ የተነሳ ፓርቲ አለ ብዬ አላምንም። ኢትዮጵያ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሲዳማ፣ ጉራጌ፣ ኮንታ፣ ሀድያ፣ አፋር ፣ ሶማሌ፣ ትግሬ እያለ ኢትዮጵያ እስላም፣ ኢትዮጵያ ክርስቲያን ነች ካላለ ኢትዮጵያ አንድናት ማለት አይቻልም። አፄ ቴዎድሮስም ቢሆን በጀግንነቱና ወንድነቱ እኛ ኢትዮያውያን ብቻ ሳይሆን መላ አፍሪካ ሊኮራ ይችላል። ነገር ግን እንደ ኦሮሞና ደቡብ ከእሳቸው ጋር አንተዋወቅም። አቢሲኒያ ማለት ቀርቶ ደቡብን አጠቃሎ ኢትዮጵያ ከተባለች በኋላ ነው መተዋወቅ የጀመርነው።
ሰንደቅ፡- እንደ አንድ የፖለቲካ ልሂቅ “ኢትዮጵያ የሶስት ሺህ ታሪክ አላት” መባሉን አይቀበሉትም ማለት ነው?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- አቢሲኒያ የሚባል ሀገር ነበር። ምናልባት ሶስት ሺው ከዚያ ጋር ተያይዞ ሊገለፅ ይችላል። የዛሬው ደቡብ፣ ምስራቅ ምዕራብ አቢሲኒያ አልነበረም። እርግጥ እንደ ሕዝብ የሚጋራው ነገር ሊኖር ይችላል። አመጋገብ፣ ባህል፣ ኪነጥበብ፣ ወንዝ ይጋራል። ነገር ግን አገር ማለት ምን ማለት እንደሆነ አናውቅም። እኛ የምናውቀው ጎሳ ነበር። ሰሜኖቹ አፄ ቴዎድሮስ ታላቅ መሪ ነበሩ፤ ከአፍሪካም ለመጀመሪያ ጊዜ ፈረንጅን የተቋቋሙ ስለሆኑ በታሪካቸው እንኩራ ቢሉ ደስ ይለኛል። ነገር ግን አፄ ቴዎድሮስ እንኳንስ ከሰሜን አልፈው ቦረና ድረስ ሊደርሱ ቀርቶ ከጎንደርም አልፈው ሰሜን ሸዋም አይታወቁም ነበር። ይህ ሲባል ግን ሸዋን ለማስገበር ጥረት አላደረጉም ማለት አይደለም። ከአፄ ቴዎድሮስ በኋላ የመጡት አፄ ምኒልክ ከሸዋ ተነስተው ሀረር ድረስ ሄደዋል። ከዚያም በኋላ ጅማና ወለጋ ድረስ እሳቸውም ባይሄዱ ወኪሎቻቸውን፣ እነ እራስ ጎበናን በመላክ ዛሬ የምናውቃትን ኢትዮጵያን ፈጥረዋል። እና ከዚያ ጊዜ በኋላ ነው ኢትዮጵያ የተፈጠረችው። በዚያም ጊዜ ቢሆን ሁሉም ኢትዮጵያውያን በፍቅርና በደስታ ኢትዮጵያን ተቀላቀሉ ማለት አይደለም። ነገሩ ሁሉ የሆነው በጉልበት ነው። በእርግጥ ጀርመንም፣ ጣሊያንም ይሄው ልምድ በመኖሩ በዚህ ላይ እኔ ቅሬታ የለኝም። እንደውም ትክክል ነው።
ሰንደቅ፡- አንድነት ፓርቲ ኢትዮጵያን በብሔር፣ በጎሳ መከፋፈል ለሀገሪቱ አንድነት አደጋ ነው በማለት በብሔር መደራጀት ዲሞክራሲያዊ መብት ቢሆንም አደረጃጀቱ ግን አይጠቅምም የሚል አቋም አለው እና. . . .?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- ብሔር የሚለውን ነገር እንተው ማለት እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲዳሞ “ሲዳሞ” መባሉን ይተዋል? አማራስ ቢሆን “አማራ” አልባልም ይላል? የሚል አይመስለኝም። ማንም ሰው ታሪኩንና ቋንቋውን ተከትሎ “እኔ እንዲህ ነኝ” ቢል ምን ችግር አለው። ችግር የሚሆነው “እኔ እንዲህ ነኝ” የሚለው ለመለያየትና ለመጣላት በር እንዲከፍት ያደረግነው ሲሆን ነው። መድረክ ቅይጥ ቢሆን ምን ችግር አለው። ልዩነታችንን አምነን በቆየን ቁጥር ጥንካሬአችንም አስተማማኝ ይሆናል። ልዩነታችንን ለወዳጅነት ካልተጠቀምንበት ጠላት እንድንሆን ሊያደርገን ይችላል። ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ ወዘተ የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት ነው። ኢትዮጵያ እንደ አንድ መኪና ብትመስላት መኪና ሊሽከረከር የሚችለው ሁሉም አካላቶቹ ሲሰሩ ነው። ኢትዮጵያም ወደፊት ልትራመድ የምትችለው ሁሉንም ሕዝቦቹን መጠቀም ስትችል ነው። ስለዚህ ቡልቻ “አንድነት አማራ አለ” እያሉ ከማኩረፍ ተቻችለን፤ ለምንስ እንዲህ አለ እያሉ በቅንነት እየፈተሽን ወደፊት መራመድ ይሻላል።
ሰንደቅ፡- በእርግጥ እርስዎ የአንድነት ፓርቲን “የአማራ ፓርቲ” ያሉበት መነሻ ምንድ ነው? ለዚህ አባባልዎት ማረጋገጫ አቅርቡ ቢባሉ ምን ሊያቀርቡ ይችላሉ?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- በመጀመሪያ ደረጃ ስለአማራ ብሔር ምንም መጥፎ ነገር አልተናገርኩም። ያልኩት ምንድነው መድረክ ውስጥ አንዳንድ ፓርቲዎች የገንዘብ ጉልበት አላቸው፤ ምክንያቱም አሜሪካን ሀገር ያለ ኢትዮጵያዊ አማራም ሆነ ኦሮሞ እንዲሁም ሲዳማና ትግሬ የኢትዮጵያ ፓርቲ አንድ ይሁኑ በሚል በአጋጣሚ አንድነት ፓርቲ ስላወቁ ለአንድነት ፓርቲ ገንዘብ ይልካሉ። እና እኔም በጽሁፉ “አንድነቶች ገንዘብ አለን ብላችሁ አትቁሙ ፤ ከሌሎቹ ተደባለቁ፣ ባገኛችሁት ገንዘብ ሁላችንንም ያሳተፈ ስብሰባ እንጥራ፣ በጋራ ቢሮ እንከራይ ብያለሁ። ምክንያቱም የመድረክ አባል ፓርቲዎች እንደ አንድት ገንዘብ የላቸውም። እናም አንድነቶች የምታገኙትን ገንዘብ ለአንድታችን አውሉ ብያለሁ። ምክንያቱም መድረክ ብቻ ነው የኢትዮጵያን ወገኖች ያሰባሰበው፤ ሰው በአግባቡ አልተገነዘበውም እንጂ መድረክ ኃይለኛ ስራ ነው የሰራው። ማንም ተነስቶ ሰልፍ ቢጠራ ዋጋ የለውም።
ሰንደቅ፡- መድረክ ለአራት ዓመታት ቢቆይም አባል ፓርቲዎቹ በፌዴራሊዝም እና በመሬት ባለቤትነት ጉዳይ ላይ መስማማት ባልቻሉበት ሁኔታ እንዴት መቀጠል ይችላሉ?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- ተሳስተሃል። በኢትዮጵያ ሁለትን ብሔራዊ ቋንቋ ይኑር ብሎ መድረክ ተስማምቷል። መድረክ መሬት አይሸጥም ብሎ ተስማምቷል፣ መድረክ የፌዴራሊዝም የመንግስት አስተዳደርን እንደሚቀበል አረጋግጧል። ለዚህ ሁሉ የተፃፈ ሰነድ አለ። አሁን አንዳንድ የአንድነት ሰዎች በአቋራጭ ሌላ ነገር እያደረጉ ነው። አዝናለሁ ሁሉም ወዳጆቼ ናቸው። ነገር ግን እኔ የምናገረው ለአንድነታችን፣ ለጥንካሬያችንና ለአሸናፊነታችን አንድ መሆን አለብን በማለት ነው። ቡልቻ “አማራ” የሚለውን ቃል ተጠቀመ ብለው ሊከፋቸው አይገባም። ታዲያ እኔ ምን ብዬ ልግለጣቸው? እዛ ያሉትን እኔ የማውቃቸው በአማራነታቸው ነው። ይሄን ቃል መናገሬም አማራን ለመውቀስ አይደለም። እንደውም አንድነቶች በመድረክ ውስጥ መኖራቸው በጣም ጥሩ ነው። ደቡቦች እና ኦሮሞዎች በአገዛዝ ውስጥ አልነበሩም። በአንድነት ውስጥ ያሉ አማራዎች ግን የጀነራል፣ የሀገረ ገዢ፣ የአምባሳደር የአስተማሪና የሲቪል ሰርቪስ ልጆችና የልጅ ልጆች ናቸው። በተዋረድ የገዢዎች ልጆች ናቸው። እና እነዚህን ሰዎች በመድረክ ውስጥ ልንጠቀምባቸው ይገባል። ቢሰድቡን እንኳ ችለን ወደነሱ መቅረብ ይገባናል። እና አማራ ነን የምትሉ ሰዎች አባካችሁ መድረክን አታዳክሙ በማለቴ “አማራ” የምትል ቃል በመግባቷ ትርጉሙ ተዛብቷል። የከተማ ሊህቃን ያልኩትም ትክክል ነው። ይሄ ደግሞ ሊያስከፋቸው አይገባም። በዚህ አገር የከተማ ሊህቃን ከሚባሉ አንዱ እኔም ልሆን እችላለሁ። በዚህ ለምን ይከፋሉ ፤ አልጠላዋቸው፣ አልቀናሁባቸው እና ገዢ ተገዢ እያልን መናናቁን ትተን ለሀገራችንና ለራሳችን ማሰብ አለብን። አፄ ኃይለስላሴ ትክክለኛዋን ኢትዮጵያ እየገለፁ ቢመሩ ኖሮ የሀገራችን አንድነት ከብረት በላይ በጠነከረ ነበር።
ሰንደቅ፡- በነገሮዎት ላይ አፄ ኃይለስላሴ “የኦሮሞ ተወላጅ ናቸው” ስለሚባለው ነገር የሚያውቁት ነገር አለ?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- እንደው በዋዛ የሚነገር እና ቁም ነገር የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የማንንም ደም መርምሮ የሚያውቅ ሰው የለም። ሕዝቡ እንደሚያምነውና እንደሚያውቀው የራስ መኮንን ጉዲሳ ልጅ ናቸው ይባላል። አቶ ጉዲሳ ደግሞ ዶባ ሰሜን ሸዋ ውስጥ የሚነሩ ኦሮሞ ናቸው። እና አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞነት አለባቸው ይባላል። ኦሮሞነት ስላላቸው የኦሮሞን ታሪክና ባህል አላቸው ማለት ግን አይደለም።
ሰንደቅ፡- አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞኛ ቋንቋ ይናገሩ ነበር?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- እኔም አነጋግሬአቸው አውቃለሁ። አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞኛ ቋንቋ በደንብ ይችላሉ። ነገር ግን ሀረር እንደኖሩ አማራዎች ነበር ኦሮምኛን የሚናገሩት። ይሄ ደግሞ የጠራ ኦሮምኛ አልነበረም።
ሰንደቅ፡- አንድነት ፓርቲን ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እንደሚመሩት እያወቁ፣ በስራ አስፈፃሚ እና በብሔራዊ ምክር ቤት ውስጥ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች መኖራቸውን እያወቁ “አንድነት ፓርቲን የአማራ ፓርቲ ማለትም የእነ ዶ/ር ነጋሶን ሞራል መጉዳት አይሆንም?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- የአንድነት ፓርቲ የአማራ ፓርቲ ናቸውና እንጥላቸው ነው ያልኩት? ይሄስ ቢባል ምን አለበት (Identification) ያስፈልጋል። ማንም ሰው ማንነቱ መታወቅ አለበት። ዶ/ር ነጋሶ እኔ በማምነው ሁኔታ ወደ አንድነት የገቡት በእርግጥ እሳቸው የሄዱበትና እኔ የምሄድበት የአንድነት መድረክ የተለየነው። እሳቸው አማራም ቢሆኑ ውስጡ ገብቼ አንድነትን አጠናክራለው የሚል አቋም አላቸው። እኔ ደግሞ በብሔራችን የፈጠርናቸው ፓርቲዎች ስላሉ እነሱን ይዘን እንግባ ያልኩት። እና ዶክተር ነጋሶ በውስጡ ገብቼ ሲሉ እኔ ከውጪ ወደውስጥ በሚል ስለሆነ ሞራላቸው የሚጎዳ አይመስለኝም።
ሰንደቅ፡- እንደሚያውቁት ባለፉት ሃያ ዓመታት በአማራ ሕዝብ ስም የመላው አማራ ሕዝብ ደርጅት (መዐሕድ) ውጪ ሌላ ፓርቲ በሕዝቡ ስም ሲመሰርት አይታይም። የክልሉ ተወላጆችም በአመዛኙ በኢትዮጵያዊነት ስም በሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ውስጥ ሊሳተፉ ይስተዋላል። እርስዎ ይሄንን ነገር አይተውታል?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- እውነትህን ነው። ይሄ ዝንባሌ ጎድቶናልም ጠቅሞናልም። ጉዳቱ እንደ የአማራ ስብስብ ፈንጠር ብለው “እኛ ነን መሪ” ብለው ባለመነሳታቸው ጥሩ ስራ ሰርተዋል ማለት ይቻላል። ነገር ግን “በሁሉም ነገር እኛ ነን ቀዳሚ” ብለው ፓርቲ መስርተው ቢነሱ የቀረው ሕዝብ ይሸሻቸዋል። የአሁኑንንም ያል አይጠጋቸውም። በወለጋ፣ በሲዳሞ፣ በሀረር አይመርጡም። እንደዚህ ካሉ ወደድሮ ገዢ መደብ እንመለሳለን። ስለዚህ ብልጠታቸውን አደንቃለሁ። “የመላ አማራ” ተብሎ ፓርቲ ሲቋቋም ሰው ሁሉ ተሳቀቀ። ምክንያቱም ሸዋ ላይ አማራውና ኦሮሞው ተደባልቋል። እናም ፓርቲው ብዙም አልገፋበትም። አሁንም ደግሜ የምናገረው “አማራ” አትበል ቢሉኝም የድሮ ገዢ መደብ ልጆች ዛሬ ለእኛ ጠቃሚ ናቸው ብዬ አምናሁ። ለምን ብትል የገዢ መደብ ልጆች በመሆናቸው እውቀት ቀምሰዋል ይጠቅሙናል። አሁንም ከነሱ ጋር መስራት አለብን። ስለዚህ ገንዘብ ስላገኙ ብቻ ብቻቸውን መሮጥ የለባቸውም። አለበለዚያ አንድነት ፓርቲ ብቻቸውን ኢትዮጵያን ሊመስል አይችልም። አሁን ባለው፣ ድሮም በነበረው ነባራዊ ሁኔታ አንድነት አሁን ባለው አደራጀት ኢትዮጵያን መለወጥ አይችልም።
ሰንደቅ፡- ኢትዮጵያ በልዩ ልዩ ብሔር የተገነባች አንድነቷም ዲሞክራሲያዊ አንድነት መሆን ይገባዋል የሚሉ ከሆነ ለምን የኢህአዴግን ፕሮግራም አይደግፉም?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- አልደግፍም! ለምን ብትለኝ ኦህዴድን ምሳሌ ልጥቀስ ኦህዴድ ከኦሮሞ ሕዝብ ነው የተገኘው? የኦህዴድ መሪዎች በራሳቸው ፈቃድ ተነስተው የተደራጁ አይደሉም። ኤርትራ ለመዋጋት ሄደው የተማረኩ ናቸው። ስልጣን የላቸውም። ከሕዝብ የፈለቁ አይደሉም። በእርግጥ ከመንግስቱ ኃይለማርያም ጊዜ ትንሽ ይሻላሉ። ታክስ የመሰብሰብ ስልጣን አላቸው። በክልሉም ወንጀለኛን መያዝ ይችላሉ። የኦሮምኛ ቋንቋ የሚተላፍ ቴሌቭዥን ከፍተዋል። እና የኢህአዴግ ፕሮግራም ጥሩ ሆኖ ሳለ ወደ አንድ ጎን አጋደለ። ህወሐት ያለውን ኃይል፣ ሐብትና ጉልበት ሌሎቹ የላቸውም። ሰልፍ ለማሳመር የተቀመጡ ናቸው። ክህወሃት ውጪ ያሉ ድርጅቶች ታክስ ለመሰብሰብ፣ ወንጀለኛን ይዞ ፍርድ ቤት ለማቅረብ፣ የተለመደውን መንግስታዊ ስራ ይሰራሉ። ጉልበት ግን የላቸውም። መንግስቱ ወይም ስርዓቱ የሚመራው ህወሃት በመሆኑ የኢህአዴግ ፕሮግራምን እንዴት ትደግፈዋለህ?
ሰንደቅ፡- በመጨረሻ የእርስዎ ባለቤት ግብፃዊ መሆናቸው ይነገራል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ ግብፅና ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ባለው የህዳሴው ግድብ ላይ አለመግባባት ተፈጥሯል። ይህ ጉዳይ በእርስዎ ቤተሰብ ላይ ምን ስሜትን ፈጠረ?
ቡልቻ ደመቅሳ፡- ባለቤቴ ሙሉ በሙሉ ግብፃዊት አይደለችም። አባቷ የትግራይ ሰው ሲሆኑ እናቷ የግብፅ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ናቸው። መቼም ባልና ሚስት የሚያወራውን ለሌላ ሰው አይነገርም፤ ምስጢር ነው። በአባይ ጉዳይ ያለን አስተያየት ግን አንድ ነው። ግብፆች መገንዘብ ያለባቸው ኢትዮጵያ ወንዙን መጠቀም የፈለገችው ከወንዙ ላይ ቆንጥራ ነው። ምናልባት እኛ የምንወስደውን ውሃ ግብፅ የምታባክነውን ሊሆን ይችላል። እኛ ውሃውን ለሃይል ማመንጫ እንጂ ለመስኖ አይደለም። ኢትዮጵያ መብቷን መጠቀም ከፈራች ትጠፋለች። ስለዚህ የቅኝ ግዛት የውሃ ስምምነቱን ሁላችንም እየተቃወምን የግብፅን ሕዝብ ሳንጎዳ መጠቀም አለብን።
**********
Source: Sendek newspaper- June 20, 2013
Thanks alot – your answer solved all my problems after several days struggling
Gorgeous pictures, Loran… What a beautiful place. the reflection in the first picture is great… AND –I love that little canhl/siebter.How was your weather up there?Hugs,Betsy
Ato Bulcha i have respect for you and all what you suggest is true and keep it up. but the sendek report about tedy afro is shame for oromo people
is really sendek newspaper ?
tedy > Oromo people ……………………………………
…………………………………………………..why?
Amaara jechuun afaan amaaraa kan dubaatu qofaa mitiim jara kenyaa afaan Oromoo utuu dubaatuu kan nu awalaa jirutu jira.Kanaafuu fali Kenya inni gudaan waqayyon kadhachuudhaa.
@The Visionary aka the dead tyrant milas Seytanawi(meles Zenawi)
i quote you “His ideas are all implications of hate and feeling of blame towards ”amhara” people for historical misdeeds of their forefathers” -that is how tplf came to power by portraying us Amharas(my beloved people as i am from Bet Amhara) as chauvinists, imperialists, dominators…etc any name that makes us feel guilty, and making the galla tribe like bulicha happy as a little child that needs taking care of! Does the dead tyrant tells us what happened in the 16th when the fucken galla tribe was roaming the territory of fatagar,Gurage,dowaro,Enarya,Shewa…etc? instead of blaming us the Amhara conquering the south in the 19th century? Or he does not read history books? Yes, that venom words were in the dead tyrants mouth whenever he speaks of the past ills of the country while portraying his golden tribe as a victim and a benevolent group! Does he know that almost all of the tigray soldiers were destroyed as they fight the grange mohammed troops in dewaro(present day Arusi) and the tigray war lords had to recruit almost most of their soliders from sudan before the galla tribe appears on the scene? Tells us morons! Shit heads! So i say to you, stay away from us because the more you lie the more you pay for it when you loose the string
P.S. it is not the debteras fabrication, you can find the details of it from the book The conquest of Abyssinia written by the Yemani Arab Faqi called Sihab ad-Din Ahmad bin And al-Qader.
@ethiopia aka kejjella(jella ras nehe)!
where did you get the statistics? from your mama’s kitchen? who cooked it for you? chaltu? people like you are morons who spite things that are fabricated to satisfy your egoistic appetite for power and domination. That is why you never had it, and you will never have it! Enjoy the stick of the weyane junta till we will take over as per our terms! You will see that we will destroy your Ethiopia and we will make it in our image! Destined to do that as the dogs bark to their grave!
Dani Boy,
One needs two minutest to know to where you belong. One thing that struck me though is the number of times you mention the word Oromo and the distorted opionion you have toward this great people. You better know ASAP that you can’t love Oromiya and hate Oromos. Do not try to label as an OLF operatives all Oromos that ask for their legitimate rights. By the way don’t you know that OLF will win/thrash OPDO if a fair and free elections were held in Oromiya today? Lemanignawum Libona Yistih
Yirga, please read other replies. Just on this blog, you can find invaluable reply from other bloggers.
I strongly doubt the cognitive development of Bulcha….I’m afraid to see Mr Bulcha Demekesa as Ethiopian leader with such trivial and lower level of thinking. He is totally absorbed in ethnicity complex while trying to stand in front of United Ethiopia. He is totally a failure. B/c he tried to deny history while his inner knows the fact. And I think he gave such fallacious and completely false analysis just to get few flawed and fundamentalist Oromos’ support rather than to give political analysis that our country is in need of……From Now on, I don’t want to read whatever Bulcha says or write since it spoils my view of Ethiopia and moreover it doesn’t have any substance to tell Ethiopian!! Bye Bye ….he (Bulcha) deceived us so far!!
If Hailesillasse committed a crime you need to accuse him by his crime not by his oromo blood. Even if he actd like as Hitller, his oromo blood is not revocable by Abbo Bulcha because his blood given by his birth not by Abbo Bulcha supporter’s goodwill.
@Qanquree, I live in UK. My children only know few Afaan Oromo words. Their way of live, accent, culture, dressings style & language are mostly Western. Are Obbo Bulcha & his supporters tell me my children not belong to Oromo? Please grow up and think out of box!
For those who claim that Hailesellase is an Oromo, please can you tell us how Oromoness is expressed? Oromo without oromo culture, language , norm and way of life is called oromo? If somebody belive in himself, how could somebody bare his language, religne and kill his people?
What he did is what other pure Amhara rulers did. If so what makes him different from them? What Obbo bulcha said is fact but the problem with the Absynians is they believe in myth than reality.The truth of the matter is the return of old rulers means the end of ” emiye Ethiopia”.
If a person has a moral integrity that makes his/her understanding & expression free from narrow and blind support. Teso’s comments lack a moral integrity and evidence to support on Mr. Bulcha’s segregation stand on Oromo people.
Some user ‘names’ try to defend Mr. Bulcha’s statements at all cost, blindly . But non of them provide evidence to disqualify Hailesillase’s having an Oromo blood or being an Oromo. The funny thing some try to justify his position by saying if someone use different Afan Oromo accent that means the person Oromo blood is void. If you live with other, it is clear that people unintentionally inter-exchange their words, culture and languages. Denying a natural phenomena and voiding a person blood because of his/ her accent is shame.
I think kiyya is trying to say a person can be an Oromo without speaking and he provided with examples to support his position. Some user ‘names’ need to see things in wider range not in a village point of view.
Great Job Obbo Bulcha!! Kiyaa I think your logic is very poor and first try to understand the context before interpreting a phrase. You are claiming that you are mature. However I doubt that very much because your wards are speaking a lot about your maturity level. Was Mr. Bulcha hiring guys from Wallaga? On what ground and Capacity? Can you provide us your data for this? Now Mr. Bulcha is not there and do you think that those from your village being hired?
አየ አቶ ቡልቻ–እርሶም ከገዢዎች ልጆች ትምርት ፈለጉ? ወላጆቻቸው ምን አይነት የአመራር ስልጠና አስተምሯቸው ይሆናል ብለው አስበው ይሆን? ወይስ ከአርበን ኢላይትስ መሞዳሞድ ፈልገው ነው አቶ ቡልቻ! I appreciate Ato Bulcha’s independence but he has no coherent thinking.
helloo gashe bulecha ,yuo said hayiie selasie can not speak pure oromo because of he lived harer,as aresult he speak mixed oromo like amhara peopel that wsre lived in harer.and also you said haile selasie did not as suche applied and recogenazed culther and belief of oromo.as to your wored it mean that harerie oromos are not oromo and also haiele selasie are not oromo because the did not aware the culther of oromo. pleas brief it a litel bit…………………????????
This is all about tribalism and bad politics which doesn’t help the commons. Politician, when they think dividing people on tribe basis suit their interest they will do it without hesitation. If they think they need to go down to clan level they will do so so long as it fits with their interest. My fellow brother don’t let them wash your brain. I know history is history we can’t undo it and redo as we wish it would be. Let’s do what we think just and right, That will save the next generation at least not to dwell and fight on history as we do on the history of our fore fathers,
No one can escape from the logics on the ground. Some one said “we are in the 21st century”. What does it mean? Have we to stick ourselves to the old dennial history in the 21st century? How long we try to cover the history and identity of the peole?
@Kiyaa, if you look the direct meaning of “የጠራ ኦሮምኛ አልነበረም”, He meant what @Tola said above and it is clear and persuasive. let me clear it with example. Someone says in Afaan Oromoo “Duulaa “(which means “ዘመቻ:ጦር”) , Amhara speaking guys say it “ዱላ” to mean stick. Hararge oromos speak as to mean zemecha, other Haileseillassie may spoke as to mean stick.
I believe hiding the fact will not solve our problem. Some people try to be ignorant about the ethnics cause and it may take long to get rid off it. Ethnics wasn’t a problem for us. Let us build a new Ethiopia based on Equality, respect and mutual understanding by avoiding past glories of fake Ethiopianism.
Brother Tola, Thank you for your comment. Mr. Bulcha is one of the great Oromo’s son. As any person, he also has shortfalls.
Not me, Mr. Bulcha said ” …ሕዝቡ እንደሚያምነውና እንደሚያውቀው የራስ መኮንን ጉዲሳ ልጅ ናቸው ይባላል። አቶ ጉዲሳ ደግሞ ዶባ ሰሜን ሸዋ ውስጥ የሚነሩ ኦሮሞ ናቸው። እና አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞነት አለባቸው ይባላል። ኦሮሞነት ስላላቸው የኦሮሞን ታሪክና ባህል አላቸው ማለት ግን አይደለም። …እኔም አነጋግሬአቸው አውቃለሁ። አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞኛ ቋንቋ በደንብ ይችላሉ። ነገር ግን ሀረር እንደኖሩ አማራዎች ነበር ኦሮምኛን የሚናገሩት። ይሄ ደግሞ የጠራ ኦሮምኛ አልነበረም።” Again He said “ሕዝቡ እንደሚያምነውና እንደሚያውቀው የራስ መኮንን ጉዲሳ ልጅ ናቸው ይባላል። አቶ ጉዲሳ ደግሞ ዶባ ሰሜን ሸዋ ውስጥ የሚነሩ ኦሮሞ ናቸው።” Then he tried to disqualify “አፄ ኃይለስላሴ ኦሮሞነት” by not speaking “የጠራ ኦሮምኛ”. This shows that for Mr. Bulcha to be an Oromo: blood and language skills not good enough.
He shouldn’t used the word “የጠራ ኦሮምኛ አልነበረም” to justify ኃይለስላሴ’s noon-ኦሮሞነት. ኦሮሞ, አማራ Gurage from ሸዋ even from ደቡብ have mix in their culture, language , blood, tone of speaking and others…
Mr. Bulcha may born from a village that lack interaction with other ethnics, as a result he may speak ” የጠራ ኦሮምኛ”. Oromo’s children born in America or other place may not speak Afan Oromo at all or they may speak a little bit using English accent. As per Mr. Bulcha justification, they are not entitled ኦሮሞነት.
My stand is against his point view. These children can be American, Ethiopian and Oromo as the same time. This is not being a fool. This how we can win the world.
@Dear Hirkoo, I don’t have any complexity. I am free from any indoctrination. I didn’t say Oromos are not the same, but we have regional differences you like it or not. I am saying: the regional differences, in any aspect, it doesn’t make anyone special!
BTW I am a mature person, no one can wash my brain. Also, I don’t have any enemies. ኦሮሞ & አማራ are not enemies each other. Regimes, individuals and groups like you and me try to create enmity between the ordinary poor people for our own personal & political interest. If there is inequality in the world, we can struggle for justice, fairness and equality without creating enmity between people based on their ethnicity.
@Kiyya: Mr Bulcha was talking about Haile Silassei. Haile Sillassei was talking Afan Oromo like an Amhara grown in Hararge. He was not talking the pure Afan Oromo that Hararge Oromo speak. What does that mean? It means probably his accent was Amhara accent, his vocabulary were mixed with Amhara words and his tone of speaking were that of an Amhara than Oromo. Language is not a problem at individual level, but at national level. Hailesillassei banned Afan Oromo from being used as modern language, from being taught in schools, from being published, from being used in offices and in court. The fact that Hailesilassei knew afan Oromo doesn’t make him Oromo or Oromo’s friend.
Anyways Kiyya, don’t try to fool yourself. Oromo is never divided by region, Oromo is one and there is no region that is more Oromo than the other, Oromo is Oromo.
you said just what you think, it is not what is written. What is written is “ነገር ግን ሀረር እንደኖሩ ‘አማራዎች’ ነበር ኦሮምኛን የሚናገሩት”. He didn’t said Harar Oromo’s. You think this because you have complexity which the Amharan regime created in you. All Oromo’s are the same have this in your mind. Don’t listen what your enemies say but listen to your belongings.
Good questions and great answers!
i am very much surprised wiz all ideas from z so called ”political elite”, ato Bulcha.He himself first need to extricate himself from ”ethnicity complex” to have the stand of talking about unity.His ideas are all implications of hate and feeling of blame towards ”amhara” people for historical misdeeds of their forefathers. Zis brings nothing to Ethiopia perhaps may disintegrate it. ”May God show z right way for those short-sighted contesting politicians like u!!!!!!”
that is right,every one has to accept the equality of all human being,ethiopia is composed from 40% of oromo,23% of amhara,6% of tigray,12 % of somali , 8% of sidama & 11% of others,the main problem in our country is unequal distribution of national resource.
Are this the leading blog in Ethiopia …… shame please at least change the header , format and presentation style and put some inspiring and esthetically sound page
To the editor : What is your point fuck head ? we are living in the 21st century – There is no distinction even between white and black – you are dividing the people of one country into micro tribes . You cannot fool ethiopians anymore. The likes of you and your cronies in ethiopia who have taken over the whole country while you represent only less than 6 percent of the population can only survive through a barbaric and primitive control of 90 mill people – trust me it is not sustainable-you cannot continue like this -you better kill yourself than write about tribal politics in order to help one minority group .
Auto Bulcha, himself has a problem. He said “…it was not speaking pure Oromo language..” . That is the problem I have with him and some Oromo brothers from Welega. A person like me from Shewa , Arisi, Harer has to be created again by his ” pure Oromo” understanding. People from his area are “PURE” Shame on this idea
Even when he was HR at AIB, he used to prefer hiring individuals from his village.
“የገዢዎች ልጆች” are also humans, Mr. Bulcha!