የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)
ሰኔ 4 ቀን 2005 ዓ.ም.
የወያኔ አገዛዝ ሕዝብን ለጦርነት፤ ሀገርን ለጥቃት እያዘጋጀ ነው
የወያኔ አገዛዝ የሕዝብን ትኩረት መደረግ ካለበት ወሳኝ ትግል ለመነጠል ሲያደርገው የነበረውን ሁሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬ በተመክሮ የተገነዘበው ነው።
በቅርቡ ደግሞ ህዳሴ ግድብ በሚለው ማታለያ የለመደባቸውን ተላላዎች በዙሪያው እያሰለፈና ሕዝብንም እየዘረፈ ያለው አልበቃ ብሎት ግብጽን እየተነኮስና እየቀሰቀስ በመቀጠሉ የአባይ ውሀ አንድም ጠብታ አይቀነሰብኝም ከምትለው ከስግብግቧ ግብጽ ጋር ጦርነትን እየጋበዘ ነው። ኢትዮጵያና ሌሎች ሀገሮች በነጭና ጥቁር አባይ የመጠቀም መብታቸው የተጠበቀ መሆኑ አያክራክርም። በአለም አቀፍ ህግ መሰረትም ሌሎች ከወንዞቹ ተጠቃሚ ሀገሮች ውሃ እንዳያገኙ ማድረግ የሚፈቀድ አይደለም። አባይን በተመለከተ ተንኮለኛው የእንግሊዝ ቅኝ አገዛዝ ሱዳንና ግብጽን ብቻ ይዞ የወሰነው የውሀ ድርሻ/ክፍፍል ትክክለኛ አለመሆኑም አከራካሪ ኣይደለም — ግብጽና ሱዳን አሌ ቢሉም። ግብጽ በረሀዋን ልታለማና ሚሊዮኖችን ልታሰፍር በመፈለግ የአባይን ውሀ በተጨማሪ ደረጃ መፈለጓና የተፋሰስ ሀገሮችን ጥቅም ከቶም አላዳምጥ ማለቷም የሚደገፍ አይደለም።
ወያኔ በአሁኑ ጊዜ ትልቅ ግድብ በሌለ ገንዘብ እሰራለሁ ብሎ የተነሳው ለኢትዮጵያ አስቦ (ወያኔና የኢትዮጵያ ጥቅም ሆድና ጀርባ ናቸውና) ሳይሆን የሕዝባዊ አመጽ ነፋስ ወደሀገራችንም እንዳይነፍስ በሚል የህዝብን እይታ ለማደናገር የሸረበው ተንኮል መሆኑ ክርክርንአይጠይቅም።
በኢትዮጵያ እስከዛሬ የተሰሩት ግድቦችና ገና ያላለቀው ግልገል ጊቤ ቁጥር ሶስትንምጨምሮ ለሀገሪቷ የመብራት ሀይል ፍጆታ ከበቂ በላይ ሆነው ሳለ ዛሬም በብዙ ከተሞች መብራት በፈረቃ እየተሰጠ እንዳለ ሕዝባችን የሚያውቀው ነው። ግዙፍ ግድብ ለመገንባት መነሳትና ይህንንም ግብጽ እንደምትቃወም እየታወቀ በስልት ጉዳዩን በመያዝ ፈንታ ድንፋታና ፕሮፓጋንዳንማስቀደሙ፤ ቦንድ ብሎ ሕዝብን ማስጨነቁና ማስገደዱ፤ ሀገር ወዳድ መስሎ ለመቅረብ መፍጨርጨሩ ሕዝብን ሊያደናግር የሚችል አይደለም። የለመዳባቸው የወያኔ የገደል ማሚቴዎችና አደናጋሪዎች –በባድሜ ጦርነት እንዳየነው ሁሉ– ሀገር ልትጠቃ ነው ኡኡ በሚል ወያኔንበመታገል ፈንታ ሕዝብ እንዲደግፍና ከጎኑ እንዲሰለፍ ለማድረግ ከወዲሁ የተንኮል ቅስቀሳ፤የማደራጀት ስራና ጫጫታ ጀምረዋል። ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ይህንን በሚገባ ተገንዝቦ ውጉዝከመ አርዮስ መባል አለባቸው።
የግብጽ ሕዝብ ጠላታችን አይደለም። አንዋር ሳዳት የአባይ ወንዝ ከተገደበብን ጦርነት የግድ ይሆናል ያለውንም አንረሳውም–ዛሬም የግብጽ መሪ ተመሳሳይ አቅዋም በመውሰድ እሱም በበኩሉ ልክ እንደ ወያኔ ውስጣዊ ውጥረቱን ዘወር ለማድረግ ይፈልጋል። ተጨባጭ ሁኔታውንና አቅምን ሳያውቁ ሳይመዝኑ ህዳሴ ግድብ ይሰራል ብለው ጫጫታ ላይ ያሉት ክፍሎች ቅዠት ላይ ናቸው ።
ከግብጽ ጋር ጦርነት ቢነሳ ይህ የኢትዮጵያ ሳይሆን የወያኔ ነው – ልክ እንደ ባድሜ። 130 ሺ ዜጋ አልቆ ምን ተገኘ? ወያኔና አጫፋሪዎቹ–አንዳንዶቹ ደግሞ ተቃዋሚ ነን ሊሉም ይጥራሉ–ኢትዮጵያ በአባይ ልትጠቀም ስትነሳ በግብጽ ተጠቃች ወይም ልትጠቃ ነው በሚል ሀገር ወዳድሁሉ ተነሳ ለማለትና ለማደናገር አቅደዋል። የሚሞኝላቸው አይኖርም ማለትም አይቻልም። ለነገሩ ግብጽ ኢትዮጵያን ሊወር አይችልም– አይሮጵላኖች አስነስቶ ግድብ ተብየውን ሊደበድብ ይችላል። የሚያቆመውም አይኖርም ። ዕድሜ ለወያኔ ስንት ሚሊዮን ብር የፈሰሰበትን አየር ሃይል በትኖ በጀሌዎቹ ሞልቶት ይቀልዳል። መካላከያ ተብየው ሆኖ ሕዝብንም ከፋፍሎና አሽመድምዶ ይገኛል።
ኢትዮጵያ መብቷን ለማስከበር አቅም የላትም። ወያኔ የአሜሪካ ሎሌና ተገዢ ነው–አሜሪካ ደግሞ ግጭት ከተነሳ ግብጽን መቃወም ኣንችልም ብላ ለወያኔ አስጠንቅቃለች። የወያኔ አገዛዝ ከድጡ ወደ ማጡ ሊከተን ነው እየጣረ ያለው። ይህን መቃወም ደግሞ ለሀገራችን ደህንነትወሳኝ ነውና ወያኔና ቅጥረኞቹን ወግዱ እረፉ እንበላቸው። ዛሬ ባለንበት ሁኔታ ከግብጽ ጋር ግጭቱ ለኢትዮጵያ የሚጠቅማት አይደለም።
የኢትዮጵያ መንግሥት የለም። ወያኔ ስልጣን ሲይዝ ከግብጽ ጋር ተፈራርሞ የሀገርን ጥቅም መሽጡንም መርሳት አንችልም። ወያኔ ጫካ ሳለም በግብጽ መረዳቱንና የተከዜ ድልድይን ሊያፈርስ መሞከሩንም የምንረሳው አይደለም። ወያኔ ከስረ መሰረቱ ሀገርን ለባዕድ ሻጭ ጸረ ኢትዮጵያ ሀይል ነበረ–አሁንም ነው። ለዚህም ነው ከባዕድ ጋር የፍጥጫን ጎዳና መርጦ ሀገራችንን ለጥቃት ሊያጋልጥ እየተፍጨረጨረ ያለው። በዚህ ጸረ ኢትዮጵያዊ ጉዞው ሀገር ወዳድ ዜጎች ከቶምመቸም ልናጅበው አይገባም ። በባድሜ የወደቁ ዜጎቻችን አጥንት ያወግዘናል። በአባይ ስም አገርን ለማስጠቃት ወገንን ለማዘናጋት የታቀደውን ወያኔያዊ ሴራ በአንድነት ልናወግዝይገባል።
Source: Ethiopian People´s Revolutionary Party (EPRP)
*********
ማስታወሻ፡- ፓርቲው በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት 130,000 ኢትዮጲያውያን ወታደሮች ተሰዉተዋል ለማለት መነሻ የሆነውን የመረጃ ምንጭ ማወቅ ባልችልም የInternational Crisis Group (ICG) ግምት ግን ከሁለቱም ወገን በድምሩ 70,000 ሰው እንደሞተ ነው፡፡ የቀድሞው የጦር ሀይሎች ኤታማጆር ሹም ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሣኤ ስልጣን ከለቀቁ በኋላ በሚዲያ ተጠይቀው ሲመልሱ 17,000 ገደማ ኢትዮጲያውያን እንደተሰዉ ገልፀዋል፡፡
ስለወያኔና ግብጽ ‹ግንኙነት›ም ፓርቲው ያብራራው ነገር የለም፡፡
(ዳንኤል ብርሀነ)
yihenin yetsafew woyane irasu new. leba new!!
first i am not a member of EPRDF. second:all of you are an ethiopian? endezih aynet nigigir kand ethiopiawi party ayxebekim. assafari nachihu. koy yenante flagot silxan bicha new.mehayimoch nachihuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuuu.
Egna enkuan hunetawochn ena akemachenen tegenzben new engenebawalen blen yetenesanew yilikus enante eyawerachu gedebu tegenbto siyalk KEZHET lay endeneberachu yigebachuwal. Eskezaw gin melkam yekum enkelf yehunlachu.
ወግዱ እናንተ ቅጥረኛ ባንዶች፣ ከመቼው ፈጥናችሁ በግብጽ ተገዛችሁ? ይህንን ለመናገር ስንት ተከፈላችሁ ይሆን?! የኢትዮጵያ ሕዝብ ለእናንተ አይነቱ ተንበርካኪ አጎብዳጆች ቦታ የለውም፡፡ አቋማችሁን አስተካክላችሁ ከድህነት ለመላቀቅ ከሚደክመው ሕዝብና ይህንኑ ከሚደግፍና ከሚያተባብር መንግሥት ጎን ከቆማችሁ እሰየው የሚያሰኝ ነው፡፡
ነገር ግን ከግብፅና መሰሎቻቸው እግር ሥር ተንበርክካችሁ የእነርሱን ፍርፋሪ የምትጠብቁ ከሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ የናንተን ቃል የሚሰማበት ጊዜም ሆነ ፍላጎት የለውም፡፡ ሕዝቡ ድምፅንና መልዕክትን ለይቶ ያውቃል፣ የማን ድምጽ እንደሆን፣ ማን ተቀብሎ እንደሚያስተጋባ፣ ድምፁ ከወዴት እንደመጣ፣ አላማው ምን እንደሆን፣ ወዘተ.. እና በከንቱ ባትደክሙና የበለጠ ትዕዝብት ላይ ባትወድቁ ይጠቅማል፡፡
ኧረ አምላክ ሆይ ምነው ዝም አልክ ?????
ይህን አይነት ሰው ምነው ባንድ ሌሊት ድምጥማጣቸውን ብታጠፋቸው ልክ እንደባቢሎናውያኑ እነዚህ ግን የኛው ወገን ግን ባንዳ መሆናቸው ያሳዝናል ምናለበት ቢያልፍልን መሞት
About which Ethiopia are you talking ? “ከግብጽ ጋር ጦርነት ቢነሳ ይህ የኢትዮጵያ ሳይሆን የወያኔ ነው” You a bunch of losers how on earth this could be Woyanes fault? Using our natural resource is our natural right. I think you become jealousy on the success of EPRDF. I am not a member of EPRDF. But I appreciate what it has done so far. I know it has many assignments to do especially in the area of good governance and justice. But, given the constraints it faced what it has done so far is really wonderful. We here in Ethiopia don’t want to hear this kind of Childish comments from the so called Diasporas. Refering history and doing nothing is not the rule of the game in the 21st century. This is non of your business because you are living in the past and day dreaming. Renaissance dam is just the beginning. SHINTACHIHUN SURIYACHU LAY ATSHINU! YEGNA YENETSANET TAGAYOCH.
yejib chuhet now ager keshet yemitebek now
AYAGEBACHIHUM ZIM BILACHIHU MEKINA ETEBU , LEMEHONU ETHIOPIAN YET TAWKALACHIHU, KEDATEGNOCH. WERE KALAWERACHIHU SILEMAYANORUACHIHU NEW AYDEL, ASAFARI ZEGOCH NACHIHU ZIM BELU.
you slave ehapa party you are not Ethiopian , I am not weyane but I love my country. you & your party is evil. LEBOCH, HODAMOCH, BOQBQKA FERI FIRFARI LEKAMI SILTAN FELAGI NACHIHU ATLEAST WEYANE SERTO ASAYTUAL ENANTE GIN WERE BICHA
Siltan lemeyaz agerin asalifew kemisetu sewoch gar hibret yelenim. Ye hagerin tikim asalifo seto Ethiopian lemegzat yemifelig party…ha ha ha Dinkem Ye Ethiopia hizboch rather Ye Ethiopia Telatoch!
Please don’t make a serious mistake, don’t repeat…
Do you really want us to comment on these irrelevant, attention seeking ‘things’.. This is not fair!!
Ge’atis’ya aloku ela tetenifis…….
First, educate yourself. Countries with population of 3 million generate more than 10,000 MW.
Do you know how much is Egypt generating? Let me tell you it is more than 20000 MW.
“….በኢትዮጵያ እስከዛሬ የተሰሩት ግድቦችና ገና ያላለቀው ግልገል ጊቤ ቁጥር ሶስትንምጨምሮ ለሀገሪቷ የመብራት ሀይል ፍጆታ ከበቂ በላይ…..”
Out of touch
I thought this party is dead. Guys if you have life go back home and see how the power shortage is in critical stage. So don’t say again We don’t need a dam.
I was there in Addis last time our area didn’t have a power almost for 5 days.