(ከበደ ካሳ)
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የኢትዮጵያ መንግስት የአባይን ጉዳይ የፖለቲካ መጠቀሚያ ማድረጉን እንዲያቆም አሳሰበ፡፡
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) “ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል የቆረጠ ፓርቲ የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ መጣሉ የማይቀር ነው” በሚል ርዕስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች እንደገለፁት አባይ ከመገደቡ በፊት መፈፀም የሚገባው የዲፕሎማሲ ስራዎች አልተሰሩም፡፡
“በአባይ ላይ ግድብ ከመሰራቱ በፊት ማለቅ የሚገባቸው የዲፕሎማሲ ስራዎችና ሌሎች ጉዳዮች በውል ታይተዋል ወይ የሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢ ነው፡፡ ከነዚህም ዋነኛው በቂ የዲፕሎማሲ ስራ ያለመሰራቱና ከአባይ ተጋሪ ሃገሮች ጋር በቂና አስተማማኝ ውይይት አድርጎ ስምምነት አለመድረስ በዚህ የተነሳ ሃገሪቱ የጦርነት ስጋት ቢገጥማት ለመቋቋም በቂ ዝግጅት ያለማድረግ ይገኙበታል፡፡”
አንድነት በመግለጫው የኢትዮጵያና የግብፅ መንግስት ከፀብ አጫሪ ድርጊት ተቆጥበው በጠረጵዛ ዙሪያ ንግግሮች ላይ እንዲያተኩሩ አሳስቧል፡፡
ሁለቱም ሀገሮች የአባይን ጉዳይ ለውስጥ ፓለቲካ ማብረጃ ከማድረጋቸው እንዲቆጠቡና የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ ጉዳዩን ለፖለቲካ መጠቀሚያ ማድረጉን እንዲያቆም ጠይቀዋል፡፡
ገዥው ፓርቲና መንግስት በህዳሴው ግድብ ላይ ህዝቡን ባለቤት አላደረጉም ብሏል አንድነት በመግለጫው፡፡
“ችግሩ የሚመነጨው ገዥው ፓርቲ በአባይ ወንዝ ላይ ግድብ ለመስራት መነሳቱ ሳይሆን የአባይን ጉዳይ የኢሕአዴግ ጉዳይ ማድረጉ፤ የአባይን ጉዳይ የአንድ ግለሰብ ራዕይ ማድረጉና ከእለት ጉርሱ ቀንሶ ቦንድ እየገዛ ያለውን ህዝብ የግድቡ ባለቤት ማድረግ አለመቻሉ ነው፡፡ ግድቡ የኢትዮጵያ ህዝብ ግድብ ይሁን የኢሕአዴግ በዉል አልለዩትም፡፡”
Source: ERTA – June 14, 2013.
*************
Watch ETV news of Andinet (Unity for Democracy and Justice) party’s press conference below (Amharic).
Unity for Democracy Party Said EPRDF Should Stop Its Game (click here)
************
ስለሕዳሴ ግድብ፡- የ‹አንድነት› ፓርቲ መግለጫ [ሙሉ ቃል]
https://hornaffairs.com/2013/06/17/udj-andinet-party-statement-on-renaissance-dam/
@Dani: What is your point when you pin point only those sentences from the press conference? You know How ERTA corrupt things like Aba Dula computer virus? Are you following that? Hope you say something about it. I could not find something bad about this party.
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መንግስትና ገዢው ፓርቲ የአገሪቷን ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀማቸው አገርን አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ሊቆም እንደሚገባ ገለፀ፡፡ ከትላንት በስቲያ ፓርቲው በፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ “የኢህአዴግን ስርዓት ከቀደሙት አምባገነን ስርዓቶች ለየት የሚያደርገው ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ስልጣን መጠቀሚያ ማዋሉ ነው” ያለው አንድነት፤ ከዚህም ውስጥ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ አንዱ እንደሆነ ገልፃል፡፡ ግድቡ ከመጀመሩ በፊት ማለቅ የነበረባቸው ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ነበሩ፣ ግድቡን ከፓርቲ አጀንዳ ወደ ህዝብ አጀንዳነት ማውረድ አለበት፣ የግድቡ ስራ አንድ አካል የሆነውን የወንዝ አቅጣጫ ማስቀየር በግንቦት ሀያ ዕለት ማድረጉ ፖለቲካዊ እንጂ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የለውም፣ ያለው አንድነት ፓርቲ፤ መንግስት ለግድቡ ግንባታ ከጉሮሮው እየነጠቀ የሚወስደው ከህዝብ ስለሆነ የአባይ ግድብ ጉዳይ የህዝብ አጀንዳ እንዲሆን መንግስት ከተቃዋሚዎችም ሆነ ከሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር አገራዊ ውይይና መግባባት ላይ መድረስ እንዳለበት ፓርቲው በመግለጫው አሳስቧል፡፡
“የአንድ መንግስት ግዴታዎች የሆኑት ተግባራት መንገድ ውሃ፣መብራትና መሰል ተግባራት መዳረሻቸው የፖለቲካ ስልጣን ማራዘም ነው ያለው ፣ለፖለቲካ ፍጆታ የማይውል ንፁህ መሰረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን ፓርቲው በፅኑእንደሚያምን ገልፆ ዛሬ እንደ አዲስ ኢህአዴግ ያነሰው በአባይ ወንዝ ላይ ግድብ መስራትና ማልማት አስፈላጊነት ለዘመናት ሲነሳ የነበረ ጉዳይ እንደሆነም አስታውሷል፡፡ የአባይን ጉዳይ በተመለከተ ከአንድ አመት የተመረጡት የግብፅ ፕሬዝዳንት መሀመድ ሙርሲ ሃሳባቸው ተቀባይነት ይኑረውም አይኑረውም ከተቃዋሚዎች ጋር እንደተነጋገሩ የሱዳን መንግስት የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታት የተሻለ ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር እየጣረ እንደሆነ የገለፀው አንድነት “የኢትዮጵያ መንግስት ግን በግትርነት ማሰርና መፈረጁን በመቀጠል የሀገራዊ መግባባት አደጋ እየሆነ ነው” ብሏል በመግለጫው፡፡ በመሆኑም አንድነት አምስት ነጥብ ያለው አቋም እንዳለው አስታውቋል፡፡
የግብፅና የኢትዮጵያ መንግስት ከፀብ አጫሪ ድርጊትና ፕሮፓጋንዳ እንዲታቀቡና የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ላይ እንዲያተኩሩ፣ አባይን መጠቀም የኢትዮጵያ የተፈጥሮ መብት እንዲሆኑ እንዲታወቅ፣ ሁለቱ ሀገራት የአባይን ጉዳይ የውስጥ ፖለቲካቸው ማብረጃ ከማድረግ እንዲቆጠቡ፣ አገራዊ መግባባት አሁኑኑ እንዲፈጠር መንግስት ሀላፊነቱን እንዲወጣና የአባይ ጉዳይ የፖለቲካ መጠቀሚያ መሆኑ እንዲያበቃ የሚሉት የፓርቲው አቋሞች ሆነው ሰፍረዋል፡፡ ከመገደቡ በፊት ማለቅ የነበረችው ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? ግንቦት ሀያ ደርግ የወደቀበት የህዝብ በዓል ሆኖ ሳለ ለምን የፓርቲ በዓል ትላላችሁ? ግድቡ ሲበሰር የተቃውም አቅጣጫን ለማስቀየር ነው ስትሉ ነበር አሁንም ሁለቱ አገሮች የውስጥ ችግራቸውን ማብረጃ እንዳያደርጉት እያላችሁ ነው፣ በግብፅና በኢትዮጵያ ጉዳይ ያላችሁ ቁርጥ ያለ አቋም ምንድነው? ኢትዮጵያ በታሪኳ ለህዝብ የሚያስብ መሪ አጋጥሟት አያውቅም ብላችኋል የእነ እምዬ ምኒሊክ ውለታን ዘንግታችሁት ነው የሚሉና መሠል ጥያቄዎች ከጋዜጠኞች ተነስተው ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል፡፡
የአንድነት ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በሠጡት ምላሽ “በእኛ በኩል ሁለቱ አገሮች ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመሩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲደረግ እንፈልጋለን” ብለዋል፡፡ የሙርሲን መንግስት ተቃዋሚዎች በሠኔ ወር መጨረሻ እናስለቅቃለን በማለታቸው ሙርሲ በአባይ ጉዳይ ነገሩን፡፡ ለማረሳሳት ጥረት ማድረጋቸው የማይቀር እንደሆነ ዶ/ር ነጋሶ ጉዳዩ በአትኩሮት ታይቶ በእኛ መንግስት በኩል እልባት ሊበጅለት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ “የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችን አስታጥቀን ችግር እንፈጥራለን የሚሉት ግብፆች ስህተት የሚጀምረው የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች አለማወቃቸው ላይ ነው” ያሉት የአንድነት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በበኩላቸው ይህ አይነት አባባላቸው የግብፅ ህዝብ አስተያየት ነው ብለው እንደማያምኑ ተናግረዋል፡፡ “እንዲህ አይነት ውይይት በኢትዮጵያም ቢካሄድ የአባይ ወንዝ አቅጣጫ ተቀይሮ የኢትዮጵያን ምድር ያጠጣ የሚል ኢትዮጵያዊ አይጠፋም” ያሉት አቶ ግርማ፣ ይህ ሀሣብ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ይወክላል የሚል እምነት እንደሌላቸው አስታውቀዋል፡፡
ተቃዋሚን ማስታጠቅ በሚለው ሀሳብ ላይ አንድነት በአገር ጥቅምና በኢትዮጵያዊነት ላይ ፈፅሞ እንደማይደራደርና ሊታሠብም እንደማይገባ በአፅንኦት ገልፀዋል – አቶ ግርማ፡፡ “ግንቦት 20 እኔን አይወክለኝም” ያሉት አቶ አስራት ጣሴ ደርግ መውደቁ ጥሩ ነገር ሆኖ ከግንቦት ሀያ የሚጠበቁት ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፍትሆች ባልተሟላበትና መፍትሄ ባላገኙበት ሁኔታ ግንቦት ሀያ የፓርቲ በዓል እንጂ የህዝብ ሆኖ ህዝብን ሊወክል እንደማይችል ተናግሯል፡፡ አንድም ለህዝብ የሚያስብ መሪ የላትም በሚለው ጉዳይ ላይ እኔ አፄ ቴድሮስን ብንወዳቸውም የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ የተዋጣላቸው ነበሩ ለማለት አስቸጋሪ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “መንግስት አሁንም ቢሆን የግብፅን ጉዳይ በቸልታ ሊመለከተው አይገባም” ያሉት የአንድነት ዋና ፀሃፊ አቶ አስራት ጣሴ በዚህ ጉዳይ ላይ ተቃዋሚዎች ከዲያስፖራውና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት አገራዊ መግባባት ላይ መድረስ አለበት ብለዋል፡፡ ከግድቡ ስራ በፊት ማለቅ የነበረባቸው ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች መካከል የናይል ተፋሰስ ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ማፅደቂያ አዋጅ መፅደቅ ከነበረበት ዘግይቶ የፀደቀበት ምክንያት አንዱ ነው ብለዋል አቶ ግርማ ሰይፉ፡፡
Source: Addis Admass.
http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=12463:%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%8A%A0%E1%8C%88%E1%88%AD-%E1%8C%A5%E1%89%85%E1%88%9D-%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%8A%A8%E1%88%9B%E1%8A%95%E1%88%9D-%E1%8C%8B%E1%88%AD-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%88%9B%E1%8B%AD%E1%8B%B0%E1%88%AB%E1%8B%B0%E1%88%AD-%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%89%B3%E1%8B%88%E1%89%80&Itemid=180
some people say EPRDF shouldn‘t gain credit for the dam. What? so the gov‘t that made the planning, the fundraising and implementation of this huge project isn‘t supposed to take credit if it succeed and take blame if it fails? that’s the dumbest statement i ever heard
This is the government with the worst records in the history, with regard to keeping the national interest,But do every thing possible to keep their group benefit! they make this huge country land looked with a forest negotiation. They send many innocent Ethiopians to jail,with the cover of low of terrorism, they are corrupting this poor people,with millions of Dollars in swiz Bank ” the wiki leak”. despite all this wrong doings, the Dam is a positive thing, we should all support it, IT is ours. But we should ask them (I mean the politicians ,including the dead) to lend us some many from their swiz deposits in case we face shortage !!
it is true and we need to take it from positive side. Morsi discussed the issue with all politicians becasue it is YeHager Guday silehone. mechem Yebadimen neger aniresawum. Bizu sewoch bizu bilewal, hasabachewun setewal. mengist alisemam. mecheresha yehonewim mengis lehizibu kal endegabaw sayihon betekaraniw new. Yalekew sew gin lemin neber? leminis tewagan? wusanewunis washitew negerun? ya endihon manim ayifeligim. I personaly bvelieve that the Dam belongs to me. Be demewozie yegezahut Gidib new, yagebagnal. So whatever it is we need to know everything about it. Tekawamiwoch wusit competent ye hig sewoch yelum malet ayimesilegnim. ye enesu mikir wuyiyi ahun yemiyasifelig yimesliegnal. Endaw chfin Honen Anizilefachew. Abay ayigedeb yalu ayimesilegnim. Minim enkuan ye hizib tekawumo lemaskeyes tetekemebet yemilu poletikagnochin balikebelim. This is my Idea.
@Dani: kechalik yerasihin eyita eyechemerik bitaweta tiru yimesilegnal. Ke tesasatiku yikirta
Hey Be FG, You need to grow up.
One party should put as its own success. All people contributing to this dam. So why a party which unable to clean itself from corruption wants to claim people dream as its own.
Good points!
Ruling and opposition parties need to grow up!
Ruling party members and leaders you need to stop worship former PM Melse Zenawi. He is gone that is it. I admire him for his influence in African and World stage, though he wasted young Tigrian’s blood and soul to keep the dream of Issayas Afewerki.
In my opinion the contraction of Nile Dam shouldn’t be associated with to any political group, and it shouldn’t be directed towards any political gains. Nile is the life blood line of the ETHIOPIAN People. EPRDF or any other party shouldn’t try to declare the successful completion of the Dam as its victory rather than all ETHIOPIANS. We can disagree each other but we have to support each other when it comes to our national interest. I don’t care what Egypt wants to do, my concern is can we lift our people out of poverty? That is where the opposition has to focus on. To make sure the Dome benefit the ETHIOPIANS not few politicians. We still have to fight to bring freedom and equality in Ethiopia, while utilizing our GOD given natural resources of ETHIOPIA to built strong economic infrastructure to equally benefit our people.
ETHIOPIA WITH THE WILL OF GOD WILL PREVAIL OVER ALL ITS ENEMIES. History is our witness. We don’t want any bodies natural wealth and we don’t give up ours.
አይ ተቃዋሚ ፓርቲ! በቃ እስከዚ ጥግ ነዉ ምታስቡት?