የጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሣለኝ ቃለምልልስ ከቪኦኤ ጋር- (ክፍል 1 እና 2)

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ለመሣተፍ በተገኙበት በኒው ዮርክ ከተማ ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው መንበረ መራሂ መንግሥቱን ከተረከቡ ወዲህ ለውጭ መገናኛ ብዙኃን አካል ቃለምልልስ ሲሰጡ ይህ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ የሰጡት ልዩ ቃለ-ምልልስ የመጀመሪያቸው ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሃገር ውስጥ ጉዳዮቿ፣ በውጭ ፖሊሲዋና እንቅስቃሴዎቿ ላይ ያነጋገራቸው የቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት ኃላፊ ፒተር ኃይንላይን ለአቶ ኃይለማርያም ካቀረባቸው ጥያቄዎች አንዱ ኢሕአዴግ የሕወሓት ተፅዕኖ እንዳለበት ይነገራል – የሚል ነበር፡፡

አቶ ኃይለማርያም ለጥያቄው መልስ መስጠት የጀመሩት የኢሕአዴግን የተፈጥሮ ሂደት በመተንተን ሲሆን የጥምረቱ አባል የሆኑት አራቱ ፓርቲዎች ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ – ሕወሓት፣ ብሔረ-አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ – ብአዴን፣ የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት – ኦሕዴድ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ – ደኢሕዴን እንደአፈጣጠራቸውና በትግሉ ውስጥ እንዳሣለፉት ጊዜ ጥንካሬያቸው፣ አቅምና ልምዳቸው አንዱ ከሌላው እንደሚለይ አመልክተዋል፡፡

“ይሁን እንጂ – አሉ አቶ ኃይለማርያም – ባለፉት አሥር ዓመታት ውስጥ የተካሄደው የሕዳሴ ሂደት አዲስና የነጠረ የፓርቲውን ፖሊሲ፣ ስትራተጂና አቅጣጫ እንዲወጣ አድርጓል፡፡…” ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጠሉና “… በዚህም መሠረት ሁሉም ፓርቲዎች ወደ አንድ ንቅናቄ ገቡና አንድ ዓይነት አቅጣጫን፣ አንድ ዓይነት ልምድና የአሠራር አካሄድ በፓርቲው የውስጥ ሥርዓት አሠፈኑና ተመጣጣኝ ሊባል የሚችል ሥፍራ ያዙ፡፡ በመሆኑም በሁሉም የኢሕአዴግ መዋቅሮች ውስጥ፤ ለምሣሌ በምክር ቤቱ ውስጥ፣ በፓርቲው ጉባዔ፣ በሁሉም ኃላፊነቶችና የሥራ ምደባዎች ላይ አራቱም ፓርቲዎች እኩል ናቸው፡፡ ለዚህ እማኙ እኔ የዚህ ሂደት ውጤት መሆኔ ነው፡፡ እኔ በሕይወት ያለሁ ማሣያ ነኝ፡፡ ኢሕአዴግ በዚህኛው ወይም በዚያኛው ቡድን ተፅዕኖ ምክንያት በተ ወሰኑ ቡድኖች ወይም የጎሣ ቡድኖች ላይ የተዛባ አያያዝ አለው ብለው ለሚገምቱ ይህ የሃሰት እና ተጨባጭነት የሌለው ግምት ነው፡፡ በመሆኑም በፓርቲያችን የውስጥ ሥርዓት ውስጥ የመጀመሪያው ጉዳይ ዴሞክራሲያዊ ግንኙት ነው፡፡ የጥንካሬአችን መሠረት የፓርቲው የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ነው፡፡ ከውጭ ሆነው የሚያስቡት፤ የሚያስቡት ፓርቲውን የውስጡን ሳያውቁ ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የፓርቲውን አሠራርና ፓርቲው እንዴት እንደሚሠራ ብዥታ ላለባቸው ሰዎች ማስጨበጥ አለብን፡፡ ይህ ፓርቲ በውስጡ ዴሞክራሲያዊ ነው፤ ውሣኔዎቹና ሥራዎቹ የሚከናወኑት በዴሞክራሲያዊ አካሄድ ነው፡፡ በመሆኑም ይህኛው ወይም ሌላኛው ፓርቲ ተፅዕኖ ያደርጋል፤ ወይም ይጫናል ማለት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም አራቱም አባል ፓርቲዎች እኩል ቁጥር ያለው ውክልና አላቸው፡፡ ከፈለጉም በዴሞክራሲያዊ ሂደት የሚፈልጉት ተፅዕኖ ሁሉ አላቸው፡፡ በመሆኑም ዋናው ጠቃሚ ጉዳይ በፓርቲው ውስጥ ዴሞክራሲ አለ፤ እየሠራ ያለ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሰዎች ያላቸውን ግምት አልቀበልም፡፡ ለማሣያም እኔ የተመረጥኩት በአራቱም ፓርቲዎች ተወካዮች በሙሉ ድምፅ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በእኔ ፓርቲ በደኢሕዴን ብቻ ሣይሆን በሌሎቹም ጭምር ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ዴሞክራሲያዊ አካሄድ ባይኖረን ኖሮ ለየፓርቲያችን ወገናዊ ሆነን እንቀር ነበር፡፡ በመሆኑም የእኔ የኢሕአዴግ ሊቀመንበር ሆኜ መመረጥ ዘግይቶም የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን የዚህ ሂደት ማሣያ ነው፡፡” ብለዋል፡፡

ቪኦኤ፡- በሁለት ሺህ ሰባት በሚካሄደው ምርጫ በዕጩነት ይቀርባሉ? ማለት ከዚህ ካሁኑ የሽግግር ወቅት በኋላ የፓርቲው መሪ የመሆን ተስፋ አለዎት?

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም፡የፓርቲው ጉባዔ ከመፍቀዱ በፊት፥ ለምሳሌ ልበል፥ ፕሬዚደንት ኦባማ የፓርቲያቸው አባላት ይሁንታ ሳይሰጡ “ፕሬዚደንታዊው ዕጩ እኔ ነኝ” ማለት ይችላሉ? አይችሉም። ልክ እንደዚያው ይሄም የፓርቲው ጉባዔ የፓርቲው ሂደት የሚወስነው ነው። ምክንያቱም ዴሞክራሲያዊ ነውና። ስለዚህ ፓርቲው ያንን ዕድል የሚሰጠኝ ከሆነ እወስደዋለሁ። ካልሰጠኝ ደግሞ ሌሎች መሠራት ያለባችውን ሥራዎች እሠራለሁ ማለት ነው። የዲሞክራሲ ሂደት ስለሆነ እኔ በግሌ ተነስቼ የፓርቲው ብዙኃን አባላት ነገ የሚመጡ ጉዳዮችን በሚመለከት የሚያደርጉትን ውሣኔ እኔ አሁን ልወስነው አልችልም። ስለሆነም ይህ ለዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የሚቀርብ ጥያቄ አይደለም። የፓርቲው አባላት ግምገማቸውን አካሂደው የሚወስኑትን “ይመርጡኛል፤ አይመርጡኝም” ብሎ ከወዲሁ መተንበይ አይቻልም።

የብዝኀ ፓርቲ ሥርዓት

ቪኦኤ፡- ኢትዮጵያ ያለው የአውራ ፓርቲ ሥርዓት ነው ሲሉ ገልፀውታል። ኢሕአዲግ ሌሎች ፓርቲዎች እንዲያድጉ ለመቀበል በሚያስችልበት ደረጃ ለመለወጥ ምን ያህል ጊዜ የሚያስፈልገው ይመስልዎታል?

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም፡- ይህም በሂደት ላይ ያለ ነው። በዚህ ጊዜ ይሆናል ብዬ የተወሰነ ቀን ላስቀምጥለት አልችልም። በሂደት የሚለወጥ ነው የሚሆነው። የእኛ ፍላጎት ግን ባጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሆን ነው። ምክንያቱም በዚህች ሀገር ንቁና ይበልጥ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲዎች በወጡ

Daniel Berhane

more recommended stories