ከኢፌዴሪ መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች
የኢፌዴሪ መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አገራችንን ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት በከፍተኛ ብስለትና ብቃት ሲመሩ የቆዩት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ካደረባቸው ህመም ለመፈወስ በውጭ አገር በህክምና ሲረዱ ከቆዩ በኋላ በትላንትናው እለት ከምሽቱ 5፡40 በድንገት ማረፋቸውን ለመላው የአገራችን ህዝቦ በታላቅ ሃዘን ይገልፃል፡፡
ክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ላለፉት ሁለት ወራት በህክምና ሲረዱና በጤናቸው ላይ መሻሻል ሲታይ ከቆየ በኋላ ከትላንት በስቲያ ጀምሮ በተከሰተ ድንገተኛ ኢንፌክሽን እንደገና ህመማቸው ተባብሶ ለአስቸኳይ የህክምና ርዳታ ወደ ሆስፒታል ገብተው በህክምና ሙያተኞችም ከፍተኛ እገዛ ቢደረግላቸውም በትላንትናው እለት ከምሽቱ 5፡40 ላይ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት የሚንስትሮች ምክር ቤት ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ከድህነትና ኋላቀርነት ለማላቀቅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በቅንነትና በታማኝነት አገራቸውን አገልግለው ከፍተኛ የለውጥ ተስፋ ያሳዩንን ክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እልፈተ ህይወት ሲገለፅ በሀዘን በተሰበረ ልብ ነው፡፡ ጠ/ሚ/ር መለስ ከምንም ነገር በላይ አገራቸውንና ህዝባቸውን የሚወዱ ለዚህች አገርና ህዝብ የላቀ ራዕይ የነበራቸው መሪ ነበሩ፡፡ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ራዕያቸውን እውን ማድረግ የጀመረና አስተማማኝ ውጤት ማምጣት የቻለ ድርጅትና መንግሥት የገነቡ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ ብላ መጠራት እንድትጀምር ያደረጉ ታላቅና እጅግ አርቆ አሳቢ መሪ ነበሩ፡፡ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ አገራችን በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አቅጣጫ እንድትጓዝ ጥራት ያላቸው ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ነድፈው በብቁ አመራራቸው በገነቧቸው ድርጅትና መንግሥት አማካይነት ተግባራዊ ማድረግ የቻሉና በአገራችን በመካሄድ ላይ ያለው ታላቅ አገራዊ የህዳሴ ጉዞ በሰመረ አቅጣጫ እንዲጓዝ ያደረጉ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡
ክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ በአገራችን ህገ-መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲገነባ፣ የህዝቦች እኩልነትና የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ህገ-መንግስታዊ ዋስትና አግኝተው በተግባር ላይ እንዲውሉ በአገራችን መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና በድህነት የሚማስኑ ወገኖችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀ ተግባር የፈፀሙ፣ ኢትዮጵያን በአዲስና ፅኑ ዴሞክራሲያዊ መሰረት ላይ ያዋቀሩ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያና አፍሪካ ታላቁን የለውጥ ሃዋሪያ ልጇቸውን አጥተዋል፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያና የአፍሪካ ትንሳኤ ያበሰረው አዲስ የአመራር ትውልድ አርቆ አሳቢ መሪያቸውን በሞት ተነጥቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አገራችንን በከፍተኛ ደረጃ ለመለወጥ የሚያስችለው የታላቁ የአምስት ዓመት የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ መሃንዲስ ከመሆናቸውም በላይ ላለፉት ሁለት ዓመታት ካደረባቸው ህመም ጋር እየታገሉ የዕቅዱን ተግባራዊነት የመሩና ባሰቡት መሰረት አገራችን የጀመረችው ተከታታይ ፈጣን እድገት የማስመዝገብ ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ያደረጉ ታላቅ የህዝብ ልጅ ነበሩ፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለአፍሪካ ቀንድና ለአፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ መሪ ናቸው። ኢትዮጵያ ለሶማሊያ፣ ለደቡብና ሰሜን ሱዳን፣ ለሩዋንዳ፣ ለብሩንዲና ለላይቤሪያ ዘላቂ ሰላም ያደረጓቸውን አስተዋፅኦ ታሪክና መላ አፍሪካውያን የማይዘነጉት ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአፍሪካ ህዝቦች ድምፅ እንዲሰማ፣ አፍሪካ በንግድና በልማት፣ በዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር፣ በሰላምና መረጋጋት አቅጣጫ እንድትጓዝ ታላቁን የኔፓድ ፕሮግራም ከአፍሪካውያን የትግል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን ያመነጩና ይህን የተቀደሰ ሃሳብ በአገራቸው ውስጥ ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን በርግጥም የተለመደ አህጉራዊ ኃላፊነቷን ከውስጧ በመጀመር እንድትወጣ ያበቁ ታላቅ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ህዳሴ መሪ ነበሩ፡፡
ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በዓለማችን ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ስርዓት እንዲዋቀር የታዳጊ አገሮች ድምፅ በመሆን፣ በዓለም አደባባይ የተሟገቱና ተቀባይነት ያተረፉ፣ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡ በዓለማችን የተፈጥሮ ሃብት ሚዛን እንዲጠበቅ፣ በቃላቸው መሰረት ኢትዮጵያ የአረንጓዴው ልማት ሃሳባቸው ተግባራዊ ማሳያ እንድትሆን ያደረጉ ታላቅና በሳል መሪ ነበሩ፡፡ በብስለታቸውና በአርቆ አሳቢነታቸው በአገራችን የበራውን የተስፋ ሻማ የለኮሱ ኢትዮጵያንና መላውን የጥቁር ማህበረሰብ ያኮሩ፣ መላው ዓለም ብቃታቸውን የመሰከረላቸው ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡
የኢፌዴሪ መንግስት የሚኒስትሮች ምክር ቤት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ህልፈተ ህይወት ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለማችንም አንድ አርቆ አሳቢ አእምሮና የለውጥ ኃይል እንዳጣች በፅኑ የሃዘን መንፈስ ይገነዘባል፡፡
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦችና
የኢትዮጵያ ወዳጆች
በክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ አለጊዜ መሞት የኢፌዴሪ መንግስት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአገራችን አስተማማኝ ዴሚክራሲያዊና ልማታዊ ህገ መንግስታዊ ስርዓት ገንብተው በማለፋቸው ደግሞ በከፍተኛ ደረጃ ይፅናናል፡፡ የጠ/ሚ/ር መለስ የለውጥ ሃሳቦች ዛሬ የ80 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ሃሳቦች ሆነዋል፡፡ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጅምራቸው በመላ አፍሪካዊያን ዘንድ አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ፣ ለለውጥና ለተሻለ ህይወት መነሳሳትን ፈጥሯል፡፡
የጠ/ሚ/ር መለስ ፖሊሲና ስትራቴጅዎች መቼም ቢሆን ደከመንም በማያውቁ የትግል አጋሮቻቸውና ድርጅታቸው እንዲሁም በልማታዊ መንግስታችንና በመላ የአገራችን ህዝቦች ንቁ ተሳትፎ በከተማና በገጠርም በተግባር ተተርጉመው አገራችንን በፍጥነት ለመለወጥ የሚያስችሉ ፍቱን አቅጣጫዎች መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ ታላቁ መሪያችን ዛሬ ከጎናችን ቢለዩም ትተውልን የሄዱት ህገ-መንግስታዊ፣ ልማታዊና ዴሞክራዊያዊ ስርዓት ከአለት በፀና መሰረት ላይ የተገነባ በመሆኑ በታላቁ መሪያችን ምንጊዜም ቢሆን እንድንኮራ፣ በራሳችን ያለን መተማመን ከፍተኛ እንዲሆንና በሀገራችን በመካሔድ ላይ ያለውን የኢትዮጵያን ህዳሴ እውን የማድረግ ጉዞ መቼም ቢሆን እንደማይቀለበስ አረጋግጦልናል።
ኢትዮጵያ ታላቋን መሪዋን በማጣቷ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ብትሆንም የ/ጠ/ሚ/ር መለስ ብሩህ አእምሮ ያፈለቃቸው መሰረታዊ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተጠናክረው ተግባራዊ መሆን ይቀጥላሉ፡፡ በህገ-መንግስታችን የተከበሩ የግልና የቡድን መብቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰፍተውና ጎልብተው ይቀጥላሉ። በሀገራችን የተጀመረው የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ በጠ/ሚ/ር መለስ ፈለግና ራዕይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድና በአፍሪካ በመጫወት ላይ ያለችው ገንቢ፣ ሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ሚና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከመሆኑም በላይ ሀገራችን ዛሬም እንደትላንቱ የመልካም ጉርብትና አብነት ሆና ትቀጥላለች፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬም እንደ ትላንቱ በአፍሪካ ህብረትና በዓለም አደባባይ የምትጫወተው ገንቢ ሚና ጠ/ሚ/ር መለስ ባስቀመጡት ራዕይና ፈለግ በመመራት ተግባራዊነቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች
ታላቁ የሀገራችን መሪ ክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ የመታመማቸው ወሬ ከተሰማ በኋላ የሀገራችን ህዝቦች ለመሪያችን ልዩ ልባዊ ፍቅር በማሳየትና በየእምነታቸው መሰረት በፀሎት መልካም ምኞታቸውን ሲገልፁ እንደቆዩ በከፍተኛ አድናቆት ተገንዝቧል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት መላ የሀገራችን ህዝቦች በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከመንግስት ጎን ተሰልፈው ሀገራቸውን በተረጋጋ ሰላማዊና ትክክለኛ አቅጣጫ ለማስቀጠል ላደረጉት ከፍተኛ ትግል ያለውን አድናቆት እየገለፀ ከእንግዲህም ሀገራችንን ከዚህ አስቸጋሪ ነገር ግን በአስተማማኝ ሁኔታ ከምናልፈው ወቅት ባሻገር ለዘላቂ እድገቷ፣ ሰላሟና የህዝብ ተጠቃሚነት እጅ ለእጅ ተያይዘን በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ እንድትንቀሳቀስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
በርካታ የአፍሪካና የዓለም መሪዎች የታላቁ መሪያችንን ጤንነት ሁኔታ ከሰሙ በኋላ በተለያዮ መንገዶች ለላኩልን የመልካም ምኞትና የድጋፍ መግለጫ የኢፌዴሪ መንግስት የሚንስትሮች ምክር ቤት በከፍተኛ አድናቆት እንደሚመለከተውና በዚህም አጋጣሚ ኢትዮጵያ ከሁሉም ሀገሮች ጋር የፈጠረችውን መልካም ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ለመግለጽ ይወዳል፡፡
ክቡር ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ በህክምና ሲረዱ በቆዩበት ወቅት ከአጠገባቸው ሳይለዩ የተቻላቸውን ሁሉ ድጋፍ ላደረጉና የመሪያችንን ጤንነት ለመመለስ አቅማቸው የፈቀደውን ትብብር ላደረጉልን የህክምና ሙያተኞች የኢፌዴሪ መንግስት ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
የኢፌዴሪ መንግስት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የቀብር ስነ-ስርዓት የሚፈፀምበትን ሒደት በማስመልከት ቀጣይ መግለጫዎችን የሚያቀርብ ሲሆን በህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት ክቡር ም/ጠ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የሚኒስትሮች ምክር ቤት እየመሩ ይቀጥላሉ፡፡
የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች
ሀገራችን ታላቁንና አርቆ አሳቢውን መሪዋን በማጣቷ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም ኢትዮጵያውያን ከመቼም ጊዜ በላቀ ሁኔታ የጠ/ሚ/ር መለስን የለውጥና የሀገር ግንባታ ራዕይ ተግባራዊ ለማድረግ በከፍተኛ ሀገራዊ የአንድነት መንፈስ ልንረባረብ የምንገደድበት ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡ የኢፌዴሪ መንግስት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህ አስቸጋሪ ወቅት በአስተማማኝ ሁኔታ ታልፎ ሀገራችን በእርግጥም የተነደፈላትን የለውጥ ራዕይ ተግባራዊ እንድታደርግ ከመቼም ጊዜ በላቀ አንድነትና የትግል መንፈስ እንድንረባረብ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ለመላው የሀገራችን ህዝቦችና ለታላቁ መሪያችን ለአቶ መለስ ዜናዊ ቤተሰቦች መፅናናትን ይመኛል፡፡
mehiretab girmay;
i don’t know what to say.
4lossing such a great leader we are really become very sad. But wt we can do is only continueing his slogan about Great xethiopian Renaissance Dam.
yetegelagelinewun new mesinanat emitilun enate banada yebanda lijoche nefisun aymarew
giligil
you was the father of …ethipia…africa…..vision….mision….goal…civilization . god bless our land ethiopia
nagaan boqodhu ,,biyyeen sitti haa qabanooftu …. abbaa biyyaa ….abbaa ,,,misoomaa… mulata kee galmaan geenya . may you rest in peace !!!!!!!!!!!!!
i am sorry for the death of meles
We have seen so many improvements in different aspects in our country .these changes were undertaken under the rule of the PM Meles.All Ethiopians must unite and stand together for a better development of our country .We shall avoid conflicting each other & must hold good ideas forward. I believe that this is best. Indeed PM Meles is Hero and also the son of hero must do what his father done good & improve what he not done good.
Dhiigni ijoollee oromoo….
I am sorry
We love you meles we rispect you
I BELIVED ZT OUR PM MELES ZENAWI HAD DONE HIS BEST AND HE WAS SMART BUT HE ALSO HAD HIS OWN
1 – 1997 ELECTION HOW MONEY PEOPLE’S R DEAD
2 – CURRENT ISAMIC SITUATION – CONSTITUTIONAL RIGHT
3 – PEOPLES WHOM R IN PRISON WITH OUT SUUFICENT EVIDENCE
4 – PRESS ISSUE WE R SECOND DICTATOR IN Z WORLD NEXT TO ERITRIA
ZIS ALL R AT Z TIME OF OUR PM
BEST AREA CONSTRUCTION OF ROAD —-
WOMEN’S RIGHT
EDUCATION
HEALTH
PARTIALLY ON OPPOSITION PARTY EXISTENCE ,,,,
POOR
HUMANITY AREA ALMOST AT ALL
PRESS
RELIGIOUS AREA FEW YEAR BEFORE
….
We are really very very sad due 2 ur journey to the other world
The PM had done a number of things for Ethiopia especially on the environment, he is not only for the benefit of Ethiopia but also for Africa. He had a power of convincing people. As to me we lost the best precious leader that could do a number of development.Any way we have nothing to do, we only beg our God to set him in heaven
“Tagay yimotal enji tigil aymotem” gena bezu tigil yitebkenal hazenachenenem beliku linaregew yigebal. Kengdih Prime Minister Meles laymelesu hedewal behazen mezenagatachenen aydegfutem. Ye teklay ministerachenen nefs begenet yanurelen bilen Gobez wegebachenen tebek argen lesera eninesa.
To speak truely my heart sad and deeply worried about meles’s death. B/c we lost strong(special man) that who thinks for the :poor ,his country,and the whole world.
To speak truth my heart sadand deeply worried about meles’s death. B/c we lost strong(special man) that who thinks for the :poor ,his country,and the whole world.
I know he was great, as a leader Meles was able to motivate, influence and communicate what the government intends to achieve, however, i perceive some weakness specially in human rights, press freedom and the involvement of true opposition parties in political arena of the nation. but, i will never ever forget his big dream, commitment and braveness
He does huge things which we all see .He have had plan to show his people what civilized nations are practicing in their home.sorry He even don’t get his fathers age. i saw him died prematurely.sorry very sorry i found it difficult to accept his death.የተጀመረዉ አባይ አልቆ ቢሞት ምናለ ቀኑን ሁሉ ፈዘዝኩ ማመንም አቃተኝ
ባለቤቴ ከለቅሶዋ የተነሳ ልታናግረኝ አልቻለችም፡፡የገረመን ነገር ምኑም ዉስጥ የለንም
ነግር ግን እንዲሁ እንወደዉ ነበር፡፡ በመሞቱ አለቀስን መጽናናትም አቃተን፡፡
እንደ ክርስቲያን ነፍሱን እግዚአብሄር ዪማረዉ፡፡
I’m going to stop following you…..you become ETV itself
IN MY LIFE I HAVEN’T HEARD THESE KIND OF LEADER B/C HE WAS THE GIFT THE GOD AND THE GOD TAKEN HIM AGAIN THE LEFT ONE FROM THESE TO FOLLOW THE STRATEGY OF THESE GREAT MAN TO THE RENAISSANCE OF THE ETHIOPIA.
My heart cries for this man. I wish some years of happiness and rest. Mele rest in peace…
PM MELEES ZENAWI IS NOT ONLY THE LEADER OF ETHIOPIA .HE WAS ALSO THE LEADER OF AFRICA. HE WAS WAS THE LEADER OF PEACE ,HE WAS THE LEADER OF LOVE AND HE WAS BEST OF BEST AFRICAN LEADER KNOW HI IS NOT ………..GOD BLESS ETHIOPIA PEAC
I feel sad I love meles and his strategy and god will gave him his value but 4 us god gave us what a right person like before
በክቡር ጠቅላይ ሚኒስተራችን ኣቶ መለስ ዜናዊ ሞት እጅግ በጣም መራራ ሀዘን የተሰማን መሆኑን እየገለፅን ለቤታሰባቸውና ለመላው የኢትዮጵ ሕዝብ መፅናናቱን ይስጥልን ለሀገራችን እንደሳቸው ያለ ሀሳቢ መሪ አምላክ ይስጠ!!!
አባይነሽ ከአዲስ አበባ
We are shocked by our leader’s death..! We love u our PM!
በክቡር ጠቅላይ ሚኒስተራችን ኣቶ መለስ ዜናዊ ሞት እጅግ በጣም መራራ ሀዘን የተሰማን ቢሆንም ”ጀግና ኣይኖርም ታሪኩ ግን ይወረሳል” እንደሚባለው እሳቸው የተውልን የኣገራችን ራእዪ ለማሳካት አያንዳንዳችን ዜጎች ሓላፊነታችን ልንወጣ ይገባል:: ለመላው የኢትዮፕያ ህዝብና ለመላ ቤተሰቦቹ መፅናናት እንመኛለን ዮሃንስ እና ቶማስ ከሽሬ-እንዳስላሴ
….He set the standard what to offer to be Ethiopia leader , he accomplish so many but there were too many on the line, his vision was greater than anyone can imagine ….but no one know him very well , he is the man studied master & PhD while he is in PM position , he studied all the past, present & future wisdom,he pushed hard him self to see the unseen so that all Ethiopia can see it, he librate him self from material world so that others will librate automatically , he think big & dream big, he sees no one will see, he lives for others not for him self, …. If you push very hard, something will break that is what happen ….. I am just very sad . You did not lost we lost you, RIP PM meles !
PM melese zenawi is not only the leader of ethiopia, he was also the leader of africa,the leader of peace, the leader of love, the leader of tollerance, the leader of humanity, the leader of leader for ever. I wish for PM melesse parents and all ethiopian mestnanaten. i don’t know what will come next, God bless our MOTHER LAND ETHIOPIA.